Logo
FastMereja
የአይ ሲ ኤም ሲ (ICMC) ሜዲካል ሴንተር አዲስ የሕክምና ማዕከል በቱሉ ዲምቱ በይፋ አስመረቀ

​#fastmereja I ​አይ ሲ ኤም ሲ (ICMC) ሜዲካል ሴንተር ለኅብረተሰቡ ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የጀመረውን ጉዞ በማስፋት፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 (ቱሉ ዲምቱ) ያስገነባውን አዲስ የውስጥ ደዌ ሕክምና ማዕከል ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ አስመረቀ።

​ይህ አዲስ ማዕከል መከፈቱ ለቱሉ ዲምቱ፣ ለኮዬ ፈጨ፣ ለአቃቂ ቃሊቲ፣ ለሸገር ከተማ እንዲሁም አጎራባች ለሆኑ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ነዋሪዎች የሕክምና ፍላጎት ትልቅ ምላሽ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

​አይ ሲ ኤም ሲ እ.ኤ.አ በ2001 በትንሽ የልብ ክሊኒክነት ተመስርቶ፣ ደረጃ በደረጃ በማደግ አሁን የደረሰበት ደረጃ ደርሷል። አክሲዮን ማህበሩ ​ከ3,000 በላይ ባለአክስዮኖችን ያቀፈ ሲሆን ​ስመጥር የሕክምና ባለሙያዎችንና በርካታ የልዩ ልዩ ሙያ ባለቤቶችን የያዘ ነው ተብሏል።

​በሆስፒታሉ የሚገኙ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎችን (ለምሳሌ የካትላብ መሣሪያ) እና የISO ዓለም አቀፍ እውቅና ያለውን የላብራቶሪ አገልግሎት በጋራ በመጠቀም የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተነግሯል።

​በማዕከሉ ውስጥ ​የውስጥ ደዌ ሕክምና የማማከርና የሕክምና አገልግሎት፣ የላብራቶሪ፣ የራጂ እና የአልትራ ሳውንድ ምርመራ፣ ሰው ሠራሽ መተንፈሻና የነፍስ አድን መሣሪያዎች የተገጠመላቸው ዘመናዊ አምቡላንሶች፣ ደረጃውን የጠበቀ ፋርማሲ፣ ​በተጨማሪም ሆስፒታሉ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የእናቶችና የሕፃናት ሕክምና እንዲሁም የኩላሊት እጥበት (Dialysis) አገልግሎቶችን ለመጀመር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል።

​አይ ሲ ኤም ሲ አጠቃላይ ሆስፒታል የተገልጋዮችን አቅም ያገናዘበና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኑ ተነግሯል።
#ጤና መረጃ

6 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.