📚 ከ11 ዓመታት በፊት ዓለምን ያስደነገጠው የሊቢያው ግድያ... እሱ እንዴት ተረፈ?
#ethiopia | "ጓደኞቹ በISIS ሲያዙ እሱ እንዴት ቀረ? በእድል? በምክንያት? ወይስ በአጋጣሚ?"
ከ11 ዓመታት በፊት (ሚያዝያ 2007 ዓ.ም) አይኤስ (ISIS) በሊቢያ በረሃ በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመው ዘግናኝ ግድያ መላው ዓለምን ያስቆጣና ልባችንን የሰበረ ክስተት ነበር።
ዛሬ፤ ከዚያ የሞት ቀጠና በመርፌ ቀዳዳ ሾልኮ የተረፈው ዳንኤል አብርሃ፤ ያንን አስፈሪ ጉዞ እና የጓደኞቹን ሰቆቃ "ሃያ ሦስት" በሚል መጽሐፍ አስፍሮታል።
ስለ መጽሐፉ:
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከአዲስ አበባ እስከ መተማ፣ ከሱዳን እስከ ሊቢያ በረሃ፣ እንዲሁም የባሕር ላይ ውጣ ውረድ በዝርዝር ተካቷል። ዳንኤል ጓደኞቹ ለሞት ሲነዱ እሱ እንዴት እንደተረፈ፣ የደላላዎቹን ሴራ እና የመጋዘኖቹን ጉስቁልና ቁልጭ አድርጎ አቅርቦታል።
ይህ በ262 ገጾች እና በ26 ምዕራፎች የተቀነበበ የጉዞ ማስታወሻ፤ በጋዜጠኛ ቢኒያም አቡራ አርታኢነት ተሰናድቶ ለንባብ በቅቷል።
ይህንን ታሪካዊ መጽሐፍ ዛሬ፣ አርብ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዋልያ መጻሕፍት (4 ኪሎ፣ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ፣ ኢክላስ ሕንጻ፣ 4ኛ ፎቅ) እየተመረቀ ነው።
የማይረሳ ታሪክ፣ የማይቀር ምርቃት!
#twentythree #booklaunch #danielabraha #libyasurvivor #truestory #waliabooks #ethiopia #addisababa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "ጓደኞቹ በISIS ሲያዙ እሱ እንዴት ቀረ? በእድል? በምክንያት? ወይስ በአጋጣሚ?"
ከ11 ዓመታት በፊት (ሚያዝያ 2007 ዓ.ም) አይኤስ (ISIS) በሊቢያ በረሃ በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመው ዘግናኝ ግድያ መላው ዓለምን ያስቆጣና ልባችንን የሰበረ ክስተት ነበር።
ዛሬ፤ ከዚያ የሞት ቀጠና በመርፌ ቀዳዳ ሾልኮ የተረፈው ዳንኤል አብርሃ፤ ያንን አስፈሪ ጉዞ እና የጓደኞቹን ሰቆቃ "ሃያ ሦስት" በሚል መጽሐፍ አስፍሮታል።
ስለ መጽሐፉ:
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከአዲስ አበባ እስከ መተማ፣ ከሱዳን እስከ ሊቢያ በረሃ፣ እንዲሁም የባሕር ላይ ውጣ ውረድ በዝርዝር ተካቷል። ዳንኤል ጓደኞቹ ለሞት ሲነዱ እሱ እንዴት እንደተረፈ፣ የደላላዎቹን ሴራ እና የመጋዘኖቹን ጉስቁልና ቁልጭ አድርጎ አቅርቦታል።
ይህ በ262 ገጾች እና በ26 ምዕራፎች የተቀነበበ የጉዞ ማስታወሻ፤ በጋዜጠኛ ቢኒያም አቡራ አርታኢነት ተሰናድቶ ለንባብ በቅቷል።
ይህንን ታሪካዊ መጽሐፍ ዛሬ፣ አርብ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዋልያ መጻሕፍት (4 ኪሎ፣ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ፣ ኢክላስ ሕንጻ፣ 4ኛ ፎቅ) እየተመረቀ ነው።
የማይረሳ ታሪክ፣ የማይቀር ምርቃት!
#twentythree #booklaunch #danielabraha #libyasurvivor #truestory #waliabooks #ethiopia #addisababa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago