Logo
SeledaPost
በአዲስ አበባ አንዳንድ መንገዶች ላይ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ተከለከለ

​የአዲስ አበባ ፖሊስ በከተማዋ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማትና የመንገድ ግንባታ ስራ ለማፋጠን እንዲቻል፣ በተወሰኑ መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ (Parking) ሙሉ በሙሉ መከልከሉን አስታውቋል።

​📍 ክልከላው የተጣለባቸው ዋና ዋና መስመሮች፦
​ከቅዱስ ኡራኤል — በአትላስ ሆቴል (ኤድሞል) በኩል እስከ ቦሌ ብራስ።
​በአደይ አበባ ስታዲየም ዙሪያ ያሉ መንገዶች።

​🚧 የክልከላው ምክንያት፦
በእነዚህ ቀጠናዎች የሚቆሙ ተሽከርካሪዎች በግንባታው ሂደት ላይ እንቅፋት እየፈጠሩ በመሆኑና የልማት ስራው የሚጠቀማቸው ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ እንዳይገደብ ለማድረግ ነው።

​⚠️ ለአሽከርካሪዎች የተላለፈ ጥብቅ ማሳሰቢያ፦
​ክልከላው ከዛሬ ጥር 04 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል።

​በስራው ላይ ከተሰማሩ ተሽከርካሪዎች ውጭ ማንኛውም የግልም ሆነ የህዝብ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት የተከለከለ ነው።

​አሽከርካሪዎች አማራጭ የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን በመጠቀም ከአላስፈላጊ ቅጣትና እንግልት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ፖሊስ አሳስቧል።

seledadotio
seledadotio
7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.