በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ሳምንታት በማርበርግ ቫይረስ በሽታ የተያዘ ወይም ምልክቶችን ያሳየ ሰው አለመገኘቱን ጤና ሚኒስቴር ገለፀ
ሚኒስቴሩ በአሁኑ ወቅት ከተረጋገጠ የማርበርግ ታማሚ ጋር ንክኪ ኖሮት ክትትል የሚደረግለት ሰው የለም ያለ ሲሆን አሁንም ግን በሀገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ሳይዘናጉ እና ችላ ሳይሉ የማሕበረሰብ አቀፍ የበሽታ መከላከያ መንገዶችን እና የሕብረተሰብ ጤና ስጋት ተግባቦቶችን ለሚቀጥሉት ተጨማሪ 21 ቀናት በይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥሉ ጠይቋል ።
ሚኒስቴሩ አክሎም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ታማሚ ከተገኘበት ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ/ም
ጀምሮ እስከ ዛሬ ታሀሳስ 27/2018 ዓ/ም ድረስ በአጠቃላይ በበሽታው ለተጠረጠሩ 3800 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 14ቱ የማርበርግ ቫይረስ እንደተገኘባቸውም ገልፆ ከእነዚህም ውስጥ ዘጠኙ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን አምስቱ ደግሞ ከበሽታው ማገገም ችለዋል ብሏል።
ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ ሆኖ ባደረገው ርብርብና ያለሰለሰ ጥረት ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ መቆጣጠር የተቻለ መሆኑን ሚኒስቴሩ ጠቅሶ በዚህ ወረርሽኝ ምላሽ ላይ የተሳተፉ እና እየተሳተፉ ያሉ የጤና ባለሙያዎቻችን፣ የዘርፉ አመራሮች፣ አጋር አካላት እና ሁሉም የሕብረተሰቡ ክፍል ምስጋና አቅርቧል።
ሚኒስቴሩ በአሁኑ ወቅት ከተረጋገጠ የማርበርግ ታማሚ ጋር ንክኪ ኖሮት ክትትል የሚደረግለት ሰው የለም ያለ ሲሆን አሁንም ግን በሀገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ሳይዘናጉ እና ችላ ሳይሉ የማሕበረሰብ አቀፍ የበሽታ መከላከያ መንገዶችን እና የሕብረተሰብ ጤና ስጋት ተግባቦቶችን ለሚቀጥሉት ተጨማሪ 21 ቀናት በይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥሉ ጠይቋል ።
ሚኒስቴሩ አክሎም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ታማሚ ከተገኘበት ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ/ም
ጀምሮ እስከ ዛሬ ታሀሳስ 27/2018 ዓ/ም ድረስ በአጠቃላይ በበሽታው ለተጠረጠሩ 3800 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 14ቱ የማርበርግ ቫይረስ እንደተገኘባቸውም ገልፆ ከእነዚህም ውስጥ ዘጠኙ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን አምስቱ ደግሞ ከበሽታው ማገገም ችለዋል ብሏል።
ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ ሆኖ ባደረገው ርብርብና ያለሰለሰ ጥረት ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ መቆጣጠር የተቻለ መሆኑን ሚኒስቴሩ ጠቅሶ በዚህ ወረርሽኝ ምላሽ ላይ የተሳተፉ እና እየተሳተፉ ያሉ የጤና ባለሙያዎቻችን፣ የዘርፉ አመራሮች፣ አጋር አካላት እና ሁሉም የሕብረተሰቡ ክፍል ምስጋና አቅርቧል።
5 months ago