ኪም ጆንግ ኡን ፕሪሚየር ሊጉ በሀገራቸው እንዲታይ ፈቃድ ሰጡ
#ethiopia | የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሀገራቸው እንዲተላለፍ ፈቃድ መስጠታቸው ይፋ ሆኗል።
ጨዋታዎቹ የቀጥታ ስርጭት እንዳያገኙ ቀድመው እገዳ ጥለው የነበሩት ኪም አሁን ፈቃድ ሰጥተዋል።
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች አሁንም ቢሆን በቀጥታ ስርጭት ሳይሆን የማያስፈልጉ ጉዳዮች እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ይተላለፋሉ ተብሏል።
ኪም ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ በሊጉ የሚጫወቱ የደቡብ ኮሪያ ተጫዋቾች በፍጹም መታየት የለባቸውም።
የብሬንትፎርዱ ኪም ጂሶ እና እና የዎልቭሱ ህዋንግ ሂ ቻን በሊጉ የሚገኙ ብቸኛ የደቡብ ኮሪያ ተጫዋቾች ናቸው።
የ90 ደቂቃ ፍጆታ ያለው አንድ ጨዋታ ወደ 60 ደቂቃ እንዲያጥር ተደርጎ ለተመልካች እንደሚደርስም ይፋ ሆኗል።
#ebc
#ethiopia | የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሀገራቸው እንዲተላለፍ ፈቃድ መስጠታቸው ይፋ ሆኗል።
ጨዋታዎቹ የቀጥታ ስርጭት እንዳያገኙ ቀድመው እገዳ ጥለው የነበሩት ኪም አሁን ፈቃድ ሰጥተዋል።
የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች አሁንም ቢሆን በቀጥታ ስርጭት ሳይሆን የማያስፈልጉ ጉዳዮች እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ይተላለፋሉ ተብሏል።
ኪም ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ በሊጉ የሚጫወቱ የደቡብ ኮሪያ ተጫዋቾች በፍጹም መታየት የለባቸውም።
የብሬንትፎርዱ ኪም ጂሶ እና እና የዎልቭሱ ህዋንግ ሂ ቻን በሊጉ የሚገኙ ብቸኛ የደቡብ ኮሪያ ተጫዋቾች ናቸው።
የ90 ደቂቃ ፍጆታ ያለው አንድ ጨዋታ ወደ 60 ደቂቃ እንዲያጥር ተደርጎ ለተመልካች እንደሚደርስም ይፋ ሆኗል።
#ebc
9 months ago