" ተጠርጣሪው ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ሕፃኑን በመግደል ተከራይቶ ይኖርበት በነበረው የሟች ታዳጊ አያት ግቢ በሚገኝ መፀዳጃ ቤት መጣሉን ከተያዘ በኋላ በሰጠው መረጃ አስክሬኑ ተገኝቷል " - ፖሊስ
➡️ " የአርባምንጭ ነዋሪዎችን ያስቆጣ ድርጊት የፈፀመዉ ግለሰብ በጭር ጊዜ ውስጥ ተገቢዉን ፍርድ ያገኛል "
በአርባ ምንጭ ከተማ በቀን 3/3/18 ዓ/ም ናትናኤል ማይክል የተባለ በግምት የ10 ዓመት ታዳጊ ከቤት መጥፋቱን ቤተሰቦች ለፖሊስ ያሳውቃሉ።
ይህን ተከትሎ ፖሊስ ፍለጋ ይጀምራል።
ፖሊስ ከሁሉም የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመሆን ክትትልና አፕሬሽን ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ አንድ ተጠሪጣሪ ለማምለጥ ሲሞክር በቁጥጥር ስር መዋሉን የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክበበው አዳል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ተጠርጣሪው ወርቁ አሰፋ ይባላል።
ግለሰቡ በአርባ ምንጭ ከተማ ሴቻ ቀበሌ ዶሳ ቀጠና ፖሪቲ ስፕሪንግ ሆቴል ጀርባ ተከራይቶ በሚኖርበት ግቢ ውስጥ የነበረን ታዳጊ አፍኖ በመውሰድ ከወላጆቹ ገንዘብ መጠየቁንና የሕፃኑ ወላጅ እናት የተጠየቀችውን 50 ሺህ ብር በባንክ ማስተላለፏን መረጃ ማግኘታቸውን ኮማንደር ክበበው ገልፀዋል።
ግለሰቡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተምሮ የተመረቀ እንደሆነ በሚገልፅ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ምክንያት በቅርቡ ከሚሰራበት ትምህርት ቤት መባረሩን መረጃዎች እንደሚያመላክቱ ኮማንደር ክበበው ተናግረዋል።
ይኸው ግለሰብ ኢ-ሰብዓዊ በሆነ ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ሕፃኑን በመግደል ተከራይቶ ይኖርበት በነበረው የሟች ታዳጊ አያት ግቢ በሚገኝ መፀዳጃ ቤት ውስጥ መጣሉን ከተያዘ በኋላ በሰጠው መረጃ አስክሬኑ መገኘቱንም አስረድተዋል።
ግለሰቡ ይህን ሕዝብን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት ከፈፀመ በኋላ በሚኒባስ ተሳፍሮ ከከተማ ለመውጣት ሲሞክር የፀጥታ ኃይሉ ከመረጃና ደህንነት ተቋም ጋር በመሆን ባደረገው ክትትል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ፉራ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።
ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሕዝቡን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት የፈፀመውን ግለሰብ ለሕግ በማቅረብ ፈጣንና ተገቢውን ፍርድ እንደሚያሰጥም ገልፀዋል።
ሕብረተሰቡ በትዕግስት እና በመፅናናት የምርመራና የፍርድ ውሳኔዉን እንዲጠባበቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ማህበረሰቡ ፦
- መኖሪያ ቤቶችን በሚያከራይበት ወቅት፣
- የአልጋ ቤት አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት፣
- በቅጥርና ውሎች ወቅት ግለሰቦችን ህጋዊ የቀበሌ ነዋሪነት ወይም ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ መያዛቸውንና ትክክለኛ አድራሻቸውንና የመጡበት ምክንያት ፣ የሚሰሩበት ተቋም ወይም ድርጅትን በማጣራት እንዲሁም ህጋዊ ተያዥ መኖሩን በማረጋገጥ ማከራየትና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawssa
tikvahethiopia
➡️ " የአርባምንጭ ነዋሪዎችን ያስቆጣ ድርጊት የፈፀመዉ ግለሰብ በጭር ጊዜ ውስጥ ተገቢዉን ፍርድ ያገኛል "
በአርባ ምንጭ ከተማ በቀን 3/3/18 ዓ/ም ናትናኤል ማይክል የተባለ በግምት የ10 ዓመት ታዳጊ ከቤት መጥፋቱን ቤተሰቦች ለፖሊስ ያሳውቃሉ።
ይህን ተከትሎ ፖሊስ ፍለጋ ይጀምራል።
ፖሊስ ከሁሉም የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመሆን ክትትልና አፕሬሽን ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ አንድ ተጠሪጣሪ ለማምለጥ ሲሞክር በቁጥጥር ስር መዋሉን የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ክበበው አዳል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ተጠርጣሪው ወርቁ አሰፋ ይባላል።
ግለሰቡ በአርባ ምንጭ ከተማ ሴቻ ቀበሌ ዶሳ ቀጠና ፖሪቲ ስፕሪንግ ሆቴል ጀርባ ተከራይቶ በሚኖርበት ግቢ ውስጥ የነበረን ታዳጊ አፍኖ በመውሰድ ከወላጆቹ ገንዘብ መጠየቁንና የሕፃኑ ወላጅ እናት የተጠየቀችውን 50 ሺህ ብር በባንክ ማስተላለፏን መረጃ ማግኘታቸውን ኮማንደር ክበበው ገልፀዋል።
ግለሰቡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተምሮ የተመረቀ እንደሆነ በሚገልፅ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ምክንያት በቅርቡ ከሚሰራበት ትምህርት ቤት መባረሩን መረጃዎች እንደሚያመላክቱ ኮማንደር ክበበው ተናግረዋል።
ይኸው ግለሰብ ኢ-ሰብዓዊ በሆነ ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ሕፃኑን በመግደል ተከራይቶ ይኖርበት በነበረው የሟች ታዳጊ አያት ግቢ በሚገኝ መፀዳጃ ቤት ውስጥ መጣሉን ከተያዘ በኋላ በሰጠው መረጃ አስክሬኑ መገኘቱንም አስረድተዋል።
ግለሰቡ ይህን ሕዝብን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት ከፈፀመ በኋላ በሚኒባስ ተሳፍሮ ከከተማ ለመውጣት ሲሞክር የፀጥታ ኃይሉ ከመረጃና ደህንነት ተቋም ጋር በመሆን ባደረገው ክትትል በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ፉራ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።
ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሕዝቡን ያስቆጣ ዘግናኝ ድርጊት የፈፀመውን ግለሰብ ለሕግ በማቅረብ ፈጣንና ተገቢውን ፍርድ እንደሚያሰጥም ገልፀዋል።
ሕብረተሰቡ በትዕግስት እና በመፅናናት የምርመራና የፍርድ ውሳኔዉን እንዲጠባበቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ማህበረሰቡ ፦
- መኖሪያ ቤቶችን በሚያከራይበት ወቅት፣
- የአልጋ ቤት አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት፣
- በቅጥርና ውሎች ወቅት ግለሰቦችን ህጋዊ የቀበሌ ነዋሪነት ወይም ፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ መያዛቸውንና ትክክለኛ አድራሻቸውንና የመጡበት ምክንያት ፣ የሚሰሩበት ተቋም ወይም ድርጅትን በማጣራት እንዲሁም ህጋዊ ተያዥ መኖሩን በማረጋገጥ ማከራየትና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawssa
tikvahethiopia
9 months ago