4 months ago
ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርኩ ቲፓኦ (TPAO) በጥቁር ባሕር የጋራ የነዳጅ ፍለጋ ለማድረግ ተስማሙ
#ethiopia | የፈረንሳዩ የኢነርጂ ግዙፍ ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርክ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ (TPAO) በጥቁር ባሕር ውስጥ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ ለማካሄድ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ተፈራረሙ። ሰኞ ዕለት ይፋ የሆነው ይህ ስምምነት የሁለቱን ኩባንያዎች የቴክኒክ ትብብር የሚያጠናክርና በጥቁር ባሕርም ሆነ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች በጋራ ለመሰማራት የሚያስችል ማዕቀፍ የፈጠረ ነው።
ይህ ስምምነት ባለፈው ወር በቱርክ የኢነርጂ ሚኒስትር ቀርቦ የነበረውን የትብብር ሐሳብ ወደ ተግባር የለወጠ መሆኑ ተገልጿል።
የሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት ይፋ በሆነበት ወቅት፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ የዋጋ መናር ታይቷል። አሜሪካ በኢራን ላይ የባሕር ላይ እገዳ ልታደርግ ትችላለች በሚል በተፈጠረ ስጋት፣ የነዳጅ ዋጋ በ 8% ጭማሪ አሳይቶ አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ 102 ዶላር በላይ ተመዝግቧል።
ይህን ተከትሎ የዓለም አገራት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፦
በነዳጅ ዋጋ መናር ሳቢያ ለዜጎቿ የሚሆን የ 1.9 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ማቅለያ ዕርዳታ ለማድረግ አቅዳለች።
ከሰባት ዓመታት ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ነዳጅ መረከብ መጀመሯ ታውቋል ሲል የዘገበው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #totalenergies #tpao #blacksea #oilprice #energycrisis #turkey #iran #globalnews #ኢነርጂ #ነዳጅ #ጥቁርባሕር
#ethiopia | የፈረንሳዩ የኢነርጂ ግዙፍ ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርክ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ (TPAO) በጥቁር ባሕር ውስጥ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ ለማካሄድ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ተፈራረሙ። ሰኞ ዕለት ይፋ የሆነው ይህ ስምምነት የሁለቱን ኩባንያዎች የቴክኒክ ትብብር የሚያጠናክርና በጥቁር ባሕርም ሆነ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች በጋራ ለመሰማራት የሚያስችል ማዕቀፍ የፈጠረ ነው።
ይህ ስምምነት ባለፈው ወር በቱርክ የኢነርጂ ሚኒስትር ቀርቦ የነበረውን የትብብር ሐሳብ ወደ ተግባር የለወጠ መሆኑ ተገልጿል።
የሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት ይፋ በሆነበት ወቅት፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ የዋጋ መናር ታይቷል። አሜሪካ በኢራን ላይ የባሕር ላይ እገዳ ልታደርግ ትችላለች በሚል በተፈጠረ ስጋት፣ የነዳጅ ዋጋ በ 8% ጭማሪ አሳይቶ አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ 102 ዶላር በላይ ተመዝግቧል።
ይህን ተከትሎ የዓለም አገራት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፦
በነዳጅ ዋጋ መናር ሳቢያ ለዜጎቿ የሚሆን የ 1.9 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ማቅለያ ዕርዳታ ለማድረግ አቅዳለች።
ከሰባት ዓመታት ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ነዳጅ መረከብ መጀመሯ ታውቋል ሲል የዘገበው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #totalenergies #tpao #blacksea #oilprice #energycrisis #turkey #iran #globalnews #ኢነርጂ #ነዳጅ #ጥቁርባሕር
1 year ago
ሊቢያ ወደ ቀደመው ትልቅነት ልትመልስ ነዉ !
/የሀገሪቱ መንግስት/
የነዳጅ ሀብቷ እርግማን ሆኖባት በአዉሮፓዉያኑ ድጋፍና እርዳታ መሪዋን በ2011 ሙአመር ጋዳፊን ከስልጣን ካስወገደው ህዝባዊ አመጽ በኋላ ለአስር አመታት የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ብጥብጥ ስትታመስ የቆየች
ሊቢያ ከጋዳፊ ዘመን መዉደቅ በኋላ በጉያዋ የያዘችዉን የነዳጅ ሀብት ለአለም ገበያ ለማቅረብ የመጀመሪያው ዘይት እና ጋዝ ጨረታ ማዉጣቷ ተሰምቷል ።
የሊቢያ ናሽናል ኦይል ኮርፖሬሽን (NOC) ሊቀ መንበር መስዑድ ሱሌማን እንዳስታወቁት፣ ወደ 40 የሚጠጉ የብዙ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሀገሪቱ ከግጭት በኋላ ለማገገም ትልቅ ምዕራፍ ነው ተብሎ በሚታሰበው ጨረታ ላይ ፍላጎት አሳይተዋል። ሌሎችም ወደ ስራ ገብተዋል ብሏል ።
እ.ኤ.አ. በ 2024 የብሪቲሽ ፔትሮሊየም (ቢፒ) እና የጣሊያን ኢኒ ከሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለስልጣን ጋር በመተባበር በጋዳምስ ተፋሰስ ውስጥ ቁፋሮ እንቅስቃሴዎችን እንደገና ጀመሩ እና በተመሳሳይ፣ የአሜሪካው የቅባት ፊልድ አገልግሎት ኩባንያ ዌዘርፎርድ ከአስር አመታት በላይ አቋርጦት የነበረዉን በ2025 ተመልሶ ገብቷል ።
እንደ ኖክ ዘገባ ከሆነ ሌሎችም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ የነዳጅ ኩባንያዎች በሃገሪቱ ነዳጅ ለማዉጣት ፍላጎት አሳይተዋል ያለ ሲሆን የትሪፖሊ መንግስት በባህር ዳርቻ እና በባህር ዳርቻዎች መካከል በእኩልነት የተከፋፈሉ 22 የነዳጅ ማዉጫ ስፍራዎችን ExxonMobil፣ Chevron፣ TotalEnergies እና Eniን ጨምሮ ከፍተኛ የአለም ኢነርጂ ድርጅቶች እየሰጠ ነው ። ከእነዚህም ውስጥ የተወሰኑት ያልተነኩ የሃይድሮካርቦን ግኝቶች ይዘዋል ። ተብሏል ።
የሊቢያ ናሽናል ኦይል ኮርፖሬሽን (NOC) እንዳሳወቀው ከሆነ ሊቢያ በግምት 91 ቢሊዮን በርሜል ያልተነካ የዘይት እና የጋዝ ክምችቶች ይዛለች፣ ይህም ሀገሪቱን በሰሜን አፍሪካ ካሉት እጅግ በጣም ተስፋ ሰጭ - ገና ያልተጠና - የሃይል ድንበሮች አንዷ አድርጓታል።
ነገር ግን ይህን ሀብቷን ለመጠቀም ዘላቂ በሆነ የፖለቲካ መረጋጋት፣ በተሻሻለ ደህንነት እና በባለሀብቶች መተማመን አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል ።
ፍለጋን ወደ ትርጉም ያለው ምርት ለመቀየር የገንዘብ ቁርጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአስተዳደር ማሻሻያዎችን እና የመሰረተ ልማት ማሻሻያዎችን እንደሚያስፈልግ የገለፁት ሚኒስተሩ ሊቢያ ዓለም አቀፍ የኃይል ማመንጫዎችን ለመሳብ የወሰደችው እርምጃ በኢኮኖሚ ሀብቷ ላይ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ገልፀዋል ።
#የኔታ_ትዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
/የሀገሪቱ መንግስት/
የነዳጅ ሀብቷ እርግማን ሆኖባት በአዉሮፓዉያኑ ድጋፍና እርዳታ መሪዋን በ2011 ሙአመር ጋዳፊን ከስልጣን ካስወገደው ህዝባዊ አመጽ በኋላ ለአስር አመታት የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ብጥብጥ ስትታመስ የቆየች
ሊቢያ ከጋዳፊ ዘመን መዉደቅ በኋላ በጉያዋ የያዘችዉን የነዳጅ ሀብት ለአለም ገበያ ለማቅረብ የመጀመሪያው ዘይት እና ጋዝ ጨረታ ማዉጣቷ ተሰምቷል ።
የሊቢያ ናሽናል ኦይል ኮርፖሬሽን (NOC) ሊቀ መንበር መስዑድ ሱሌማን እንዳስታወቁት፣ ወደ 40 የሚጠጉ የብዙ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ለሀገሪቱ ከግጭት በኋላ ለማገገም ትልቅ ምዕራፍ ነው ተብሎ በሚታሰበው ጨረታ ላይ ፍላጎት አሳይተዋል። ሌሎችም ወደ ስራ ገብተዋል ብሏል ።
እ.ኤ.አ. በ 2024 የብሪቲሽ ፔትሮሊየም (ቢፒ) እና የጣሊያን ኢኒ ከሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለስልጣን ጋር በመተባበር በጋዳምስ ተፋሰስ ውስጥ ቁፋሮ እንቅስቃሴዎችን እንደገና ጀመሩ እና በተመሳሳይ፣ የአሜሪካው የቅባት ፊልድ አገልግሎት ኩባንያ ዌዘርፎርድ ከአስር አመታት በላይ አቋርጦት የነበረዉን በ2025 ተመልሶ ገብቷል ።
እንደ ኖክ ዘገባ ከሆነ ሌሎችም ዋና ዋና ዓለም አቀፍ የነዳጅ ኩባንያዎች በሃገሪቱ ነዳጅ ለማዉጣት ፍላጎት አሳይተዋል ያለ ሲሆን የትሪፖሊ መንግስት በባህር ዳርቻ እና በባህር ዳርቻዎች መካከል በእኩልነት የተከፋፈሉ 22 የነዳጅ ማዉጫ ስፍራዎችን ExxonMobil፣ Chevron፣ TotalEnergies እና Eniን ጨምሮ ከፍተኛ የአለም ኢነርጂ ድርጅቶች እየሰጠ ነው ። ከእነዚህም ውስጥ የተወሰኑት ያልተነኩ የሃይድሮካርቦን ግኝቶች ይዘዋል ። ተብሏል ።
የሊቢያ ናሽናል ኦይል ኮርፖሬሽን (NOC) እንዳሳወቀው ከሆነ ሊቢያ በግምት 91 ቢሊዮን በርሜል ያልተነካ የዘይት እና የጋዝ ክምችቶች ይዛለች፣ ይህም ሀገሪቱን በሰሜን አፍሪካ ካሉት እጅግ በጣም ተስፋ ሰጭ - ገና ያልተጠና - የሃይል ድንበሮች አንዷ አድርጓታል።
ነገር ግን ይህን ሀብቷን ለመጠቀም ዘላቂ በሆነ የፖለቲካ መረጋጋት፣ በተሻሻለ ደህንነት እና በባለሀብቶች መተማመን አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል ።
ፍለጋን ወደ ትርጉም ያለው ምርት ለመቀየር የገንዘብ ቁርጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአስተዳደር ማሻሻያዎችን እና የመሰረተ ልማት ማሻሻያዎችን እንደሚያስፈልግ የገለፁት ሚኒስተሩ ሊቢያ ዓለም አቀፍ የኃይል ማመንጫዎችን ለመሳብ የወሰደችው እርምጃ በኢኮኖሚ ሀብቷ ላይ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ገልፀዋል ።
#የኔታ_ትዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
Comments