4 months ago
ኢትዮ ቴሌኮም "teleSign" የተሰኘውን የዲጂታል ፊርማ መድረክ በይፋ አስጀመረ
#ethiopia | ኢትዮ ቴሌኮም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር በመተባበር "teleSign" የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ፊርማ መድረክ በይፋ ወደ ሥራ አስገብቷል።
ይህ ዘመናዊ መድረክ የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓታቸውን ወደ ዲጂታል በመቀየር ለዜጎች ቀልጣፋ፣ ግልፅና ወረቀት አልባ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ሲሆን፣ "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት የሚደረገውን ጉዞ በእጅጉ ያፋጥነዋል።
ቴክኖሎጂው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ የማንነት ማረጋገጫ (Liveness Detection) ስርዓትን የሚጠቀም በመሆኑ፣ የሰነድ መጭበርበርንና ስርቆትን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተማማኝነትን ያረጋግጣል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ፣ መድረኩ በተለይ በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያለውን ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።
እንደ አምባሳደሩ ገለጻ፣ ቀደም ሲል ዳያስፖራው የውክልና ሥልጣንና ሌሎች የሰነድ ማረጋገጫ አገልግሎቶችን ለማግኘት በአካል ኤምባሲዎች መገኘት ይገደድ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ይህ "ድንበር የለሽ ቴክኖሎጂ" ዜጎች ባሉበት ሆነው በደቂቃዎች ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲያስፈጽሙ በማድረግ እንግልትንና ወጪን በእጅጉ ይቀንሳል።
የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ በበኩላቸው፣ የዲጂታል ፊርማው በሀገሪቱ የዲጂታል ፊርማ አዋጅ መሠረት ሙሉ የሕግ ከላላና ተቀባይነት ያለው መሆኑን ገልጸዋል። የአሰራር ስርዓቱን ከሰው ንክኪ ነፃ ማድረጉ በፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ ኪኒሶ እንደገለፁት ፣ ከተቋሙ ባህላዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ዲጂታል ሽግግር የተደረገ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንና ከብሔራዊ መታወቂያ (Fayda) ጋር መገናኘቱ ማንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ፣ ኩባንያቸው ከግንኙነት አገልግሎት አቅራቢነት ወደ ዲጂታል አገልግሎት አቅራቢነት እያደረገ ያለውን ስኬታማ ሽግግር አውስተዋል።
የቴሌሳይን መድረክ የላቀ የቴክኖሎጂ ውጤቶችንና የቴሌብር (telebirr) ክፍያ ሥርዓትን በማቀናጀት ለተቋማትም ሆነ ለግለሰቦች ደህንነቱ የተጠበቀና ፈጣን ዲጂታል ምህዳር እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
ተገልጋዮች ይህንን አገልግሎት በቴሌሳይን መተግበሪያ (teleSign App)፣ በድረ-ገፅ ወይም በQR ኮድ አማካኝነት በቀላሉ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የዲጂታል ኢኮኖሚ ባለቤት እንድትሆን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiotelecom #telesign #digitalethiopia2030 #digitalsignature #telebirr #techinnovation #ethiopiadigitaltransformation
#ethiopia | ኢትዮ ቴሌኮም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከፍትህ ሚኒስቴር እና ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር በመተባበር "teleSign" የተሰኘ አዲስ የዲጂታል ፊርማ መድረክ በይፋ ወደ ሥራ አስገብቷል።
ይህ ዘመናዊ መድረክ የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓታቸውን ወደ ዲጂታል በመቀየር ለዜጎች ቀልጣፋ፣ ግልፅና ወረቀት አልባ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ሲሆን፣ "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት የሚደረገውን ጉዞ በእጅጉ ያፋጥነዋል።
ቴክኖሎጂው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ የማንነት ማረጋገጫ (Liveness Detection) ስርዓትን የሚጠቀም በመሆኑ፣ የሰነድ መጭበርበርንና ስርቆትን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተማማኝነትን ያረጋግጣል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ፣ መድረኩ በተለይ በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያለውን ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።
እንደ አምባሳደሩ ገለጻ፣ ቀደም ሲል ዳያስፖራው የውክልና ሥልጣንና ሌሎች የሰነድ ማረጋገጫ አገልግሎቶችን ለማግኘት በአካል ኤምባሲዎች መገኘት ይገደድ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ይህ "ድንበር የለሽ ቴክኖሎጂ" ዜጎች ባሉበት ሆነው በደቂቃዎች ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲያስፈጽሙ በማድረግ እንግልትንና ወጪን በእጅጉ ይቀንሳል።
የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ በበኩላቸው፣ የዲጂታል ፊርማው በሀገሪቱ የዲጂታል ፊርማ አዋጅ መሠረት ሙሉ የሕግ ከላላና ተቀባይነት ያለው መሆኑን ገልጸዋል። የአሰራር ስርዓቱን ከሰው ንክኪ ነፃ ማድረጉ በፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ ኪኒሶ እንደገለፁት ፣ ከተቋሙ ባህላዊ አሰራር ወደ ዘመናዊ ዲጂታል ሽግግር የተደረገ ወሳኝ እርምጃ መሆኑንና ከብሔራዊ መታወቂያ (Fayda) ጋር መገናኘቱ ማንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ፣ ኩባንያቸው ከግንኙነት አገልግሎት አቅራቢነት ወደ ዲጂታል አገልግሎት አቅራቢነት እያደረገ ያለውን ስኬታማ ሽግግር አውስተዋል።
የቴሌሳይን መድረክ የላቀ የቴክኖሎጂ ውጤቶችንና የቴሌብር (telebirr) ክፍያ ሥርዓትን በማቀናጀት ለተቋማትም ሆነ ለግለሰቦች ደህንነቱ የተጠበቀና ፈጣን ዲጂታል ምህዳር እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
ተገልጋዮች ይህንን አገልግሎት በቴሌሳይን መተግበሪያ (teleSign App)፣ በድረ-ገፅ ወይም በQR ኮድ አማካኝነት በቀላሉ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የዲጂታል ኢኮኖሚ ባለቤት እንድትሆን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiotelecom #telesign #digitalethiopia2030 #digitalsignature #telebirr #techinnovation #ethiopiadigitaltransformation
Comments