3 months ago
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኅብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ተጠናቀቁ
*****************
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአምስት ከተሞች የሚገኙ ከ180 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ግዙፍ የውኃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እየሆኑ ነው።
በክልሉ በ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡና ከአምስት በላይ ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ምረቃ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በተገኙበት፣ በዛሬው ዕለት በወላይታ ዞን ሆቢቻ ወረዳ የተገነባው የብዝሃ ቀበሌ ንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
ይህ ፕሮጀክት ብቻውን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን፣ ከ31 ሺህ በላይ የሚሆኑ የአካባቢውን ነዋሪዎች የንፁህ መጠጥ ውኃ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ሰሞኑን የተመረቁትን ጨምሮ በክልሉ ግንባታቸው በተከታታይ እየተመረቁ የሚገኙት እነዚህ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ ከ180 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው።
ፕሮጀክቶቹ በጌዴኦ ዞን የጨለለቅቱ ከተማ፣ በወላይታ ዞን የሆቢቻ ወረዳ ብዝሀ-ቀበሌ፣ በጋሞ ዞን የዘፍነ ከተማ፣ በደቡብ ኦሞ ዞን የቀያፈር ከተማ እና በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ የሚገኙ ናቸው።
በትናንትናው ዕለት በጌዴኦ ዞን ጨለለቅቱ ከተማ የምረቃ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን፣ ዛሬ በወላይታ ዞን ሆቢቻ ወረዳም ተካሂዷል፡፡ በቀጣይም በሌሎች ቀሪ ከተሞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ እንደሚካሄድ ታውቋል።
እነዚህ የንፁህ መጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች "የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት" አካል ሲሆኑ፣ ግንባታቸውም በፌዴራል፣ በክልልና በዞን መንግሥት እንዲሁም ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው በክልሉ በተለይም በገጠር እና በከፊል የከተማ አካባቢዎች የነበረውን የንፁህ መጠጥ ውኃ እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰው በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
በትዕግስቱ ቡቼ
#ethiopia #southethiopia #waterinfrastructure #development #cleanwater #ethiopianbroadcastingcorporation
*****************
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአምስት ከተሞች የሚገኙ ከ180 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ግዙፍ የውኃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እየሆኑ ነው።
በክልሉ በ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡና ከአምስት በላይ ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ምረቃ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በተገኙበት፣ በዛሬው ዕለት በወላይታ ዞን ሆቢቻ ወረዳ የተገነባው የብዝሃ ቀበሌ ንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡
ይህ ፕሮጀክት ብቻውን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን፣ ከ31 ሺህ በላይ የሚሆኑ የአካባቢውን ነዋሪዎች የንፁህ መጠጥ ውኃ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል።
ሰሞኑን የተመረቁትን ጨምሮ በክልሉ ግንባታቸው በተከታታይ እየተመረቁ የሚገኙት እነዚህ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ ከ180 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው።
ፕሮጀክቶቹ በጌዴኦ ዞን የጨለለቅቱ ከተማ፣ በወላይታ ዞን የሆቢቻ ወረዳ ብዝሀ-ቀበሌ፣ በጋሞ ዞን የዘፍነ ከተማ፣ በደቡብ ኦሞ ዞን የቀያፈር ከተማ እና በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ የሚገኙ ናቸው።
በትናንትናው ዕለት በጌዴኦ ዞን ጨለለቅቱ ከተማ የምረቃ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን፣ ዛሬ በወላይታ ዞን ሆቢቻ ወረዳም ተካሂዷል፡፡ በቀጣይም በሌሎች ቀሪ ከተሞች የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ እንደሚካሄድ ታውቋል።
እነዚህ የንፁህ መጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች "የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት" አካል ሲሆኑ፣ ግንባታቸውም በፌዴራል፣ በክልልና በዞን መንግሥት እንዲሁም ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው በክልሉ በተለይም በገጠር እና በከፊል የከተማ አካባቢዎች የነበረውን የንፁህ መጠጥ ውኃ እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰው በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
በትዕግስቱ ቡቼ
#ethiopia #southethiopia #waterinfrastructure #development #cleanwater #ethiopianbroadcastingcorporation
5 months ago
🛑 ከአጥፊነቱ ያልተማረው ተቋም በከባድ የገንዘብ ቅጣት ተቀጣ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ (ወረዳ 1) ልዩ ቦታው ባንቢስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ አንድ የሆቴል አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ የተከለከለ የፍሳሽ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመልቀቁ ሳቢያ ከፍተኛ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶበታል።
📌 የቅጣቱ ዝርዝር
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ባደረጉት ክትትል፣ ተቋሙ የሽንት ቤት ፍሳሽ ቆሻሻን በቀጥታ ወደ ወንዝና ወንዝ ዳርቻ ሲለቅ ተገኝቷል።
የሚገርመው ግን ይህ የመጀመሪያው ጥፋቱ አለመሆኑ ነው፦
* ተቋሙ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ድርጊት ተገኝቶ የ300 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበት ነበር።
* ሆኖም ግን ካለፈው ስህተቱ መማር ባለመቻሉ እና ድርጊቱን በመደጋገሙ፣ የአሁኑ ቅጣት እጥፍ (600,000 ብር) እንዲሆን ተወስኗል።
⚠️ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ
ባለስልጣኑ እንዳስታወቀው፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የወንዝ ዳርቻዎችን ለልማትና ለውበት እያዋለ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ እንዲህ ያሉ የብክለት ተግባራት በፍጹም አይታገሱም። መሰል ድርጊት በሚፈጽሙ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
"ውበትን ማድነቅ ብቻ ሳይሆን፣ ውበትን መጠበቅም የዜግነት ግዴታ ነው!"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #addisababa #environment #cleanwater #greencity #ethiopia #የአዲስአበባደንብማስከበር #አካባቢጥበቃ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ (ወረዳ 1) ልዩ ቦታው ባንቢስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ አንድ የሆቴል አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ የተከለከለ የፍሳሽ ቆሻሻን ወደ ወንዝ በመልቀቁ ሳቢያ ከፍተኛ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶበታል።
📌 የቅጣቱ ዝርዝር
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ባደረጉት ክትትል፣ ተቋሙ የሽንት ቤት ፍሳሽ ቆሻሻን በቀጥታ ወደ ወንዝና ወንዝ ዳርቻ ሲለቅ ተገኝቷል።
የሚገርመው ግን ይህ የመጀመሪያው ጥፋቱ አለመሆኑ ነው፦
* ተቋሙ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ድርጊት ተገኝቶ የ300 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበት ነበር።
* ሆኖም ግን ካለፈው ስህተቱ መማር ባለመቻሉ እና ድርጊቱን በመደጋገሙ፣ የአሁኑ ቅጣት እጥፍ (600,000 ብር) እንዲሆን ተወስኗል።
⚠️ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ
ባለስልጣኑ እንዳስታወቀው፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የወንዝ ዳርቻዎችን ለልማትና ለውበት እያዋለ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ እንዲህ ያሉ የብክለት ተግባራት በፍጹም አይታገሱም። መሰል ድርጊት በሚፈጽሙ ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
"ውበትን ማድነቅ ብቻ ሳይሆን፣ ውበትን መጠበቅም የዜግነት ግዴታ ነው!"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #addisababa #environment #cleanwater #greencity #ethiopia #የአዲስአበባደንብማስከበር #አካባቢጥበቃ
Comments