7 hours ago
በ2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዟል
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
1 month ago
በአማራ ክልል ከ99 ሺህ በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ይወስዳሉ
በአማራ ክልል ከ99 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ጥላሁን ወርቅነህ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ፈተና 99 ሺህ 900 ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ዘርፈ ብዙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ተማሪዎች የስነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖራቸው በስነ ልቦና ምሁራን የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ፤ ከመደበኛው የክፍል ትምህርት በተጨማሪ የማካካሻ ትምህርቶችንና ሞዴል ፈተናዎችን የመስጠት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ፈተናውን መቶ በመቶ በበይነ-መረብ ለመስጠት የታቀደውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት ክልሉ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዚህም መሠረት በየደረጃው ያሉ ኮምፒውተሮችን የመጠገን፣ አዳዲስ ግዢዎችን የመፈጸምና የኢንተርኔት መሠረተ-ልማት የማሟላት ስራዎች በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በፈተና ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይልና የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ እንዳያጋጥም ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ሌሎች አጋር አካላትን ያካተተ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ተግባር መግባቱንም አመላክተዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመማሪያ መጽሐፍ አቅርቦት ለአንድ ተማሪ አንድ መጽሐፍ በሚል ደረጃ ተደራሽ መደረጉ ለተማሪዎቹ ዝግጅት ትልቅ አቅም ፈጥሯል ሲሉ አስረድተዋል።
#ጋዜጣፕላስ
በአማራ ክልል ከ99 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ጥላሁን ወርቅነህ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ፈተና 99 ሺህ 900 ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ዘርፈ ብዙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ተማሪዎች የስነ ልቦና ዝግጅት እንዲኖራቸው በስነ ልቦና ምሁራን የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ፤ ከመደበኛው የክፍል ትምህርት በተጨማሪ የማካካሻ ትምህርቶችንና ሞዴል ፈተናዎችን የመስጠት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
ፈተናውን መቶ በመቶ በበይነ-መረብ ለመስጠት የታቀደውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት ክልሉ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዚህም መሠረት በየደረጃው ያሉ ኮምፒውተሮችን የመጠገን፣ አዳዲስ ግዢዎችን የመፈጸምና የኢንተርኔት መሠረተ-ልማት የማሟላት ስራዎች በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በፈተና ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይልና የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ እንዳያጋጥም ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ሌሎች አጋር አካላትን ያካተተ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ተግባር መግባቱንም አመላክተዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመማሪያ መጽሐፍ አቅርቦት ለአንድ ተማሪ አንድ መጽሐፍ በሚል ደረጃ ተደራሽ መደረጉ ለተማሪዎቹ ዝግጅት ትልቅ አቅም ፈጥሯል ሲሉ አስረድተዋል።
#ጋዜጣፕላስ
4 months ago
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አጀንዳውን ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረከበ
በቅርቡ ሰላማዊ አማራጭን ተቀብለው ከአማራ ክልል መንግስት ጋር የስላም ስምምነት የተፈራረሙት የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አሕፋድ) አመራሮች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያሰባሰቡትን አጀንዳን አስረከቡ።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አመራሮች ጋር አጀንዳ የማሰባሰብ መርሐግብር አካሂዷል።
በመረሐግብሩ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ከአመራሮቹ አጀንዳውን ተረክበዋል፡፡
#ጋዜጣፕላስ
በቅርቡ ሰላማዊ አማራጭን ተቀብለው ከአማራ ክልል መንግስት ጋር የስላም ስምምነት የተፈራረሙት የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አሕፋድ) አመራሮች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያሰባሰቡትን አጀንዳን አስረከቡ።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አመራሮች ጋር አጀንዳ የማሰባሰብ መርሐግብር አካሂዷል።
በመረሐግብሩ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ከአመራሮቹ አጀንዳውን ተረክበዋል፡፡
#ጋዜጣፕላስ
6 months ago
በደሞዝ ጭማሪ ሰበብ ሕገወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ርምጃ ተወሰደባቸው
የደሞዝ ጭማሪን ሰበብ አድርገው ሕገወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ርምጃ እንደተወሰደባቸው የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከደሞዝ ጭማሪ ጋር ተያይዞ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ንረት እና ቀጣይ ርምጃዎችን አስመለክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም ሙሀመድ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የደሞዝ ጭማሪን ተከትሎ የሚመጣን የዋጋ ንረት ለመከላከል የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ተጠናክረዋል።
በዚህም የደመወዝ መጨመርን እንደ ሰበብ በመጠቀም የዋጋ ንረት እንዲመጣ ባደረጉ ነጋዴዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ ርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
በተደረገ የክትትል እና የቁጥጥር ስራም የደሞዝ ጭማሪን ሰበብ አድርገው ሕገወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ርምጃ መወሰዱን አብራርተዋል።
ያለ አግባብ ዋጋ በጨመሩ፣ ምርት በደበቁ እና የምርት ጥራት አጓድለው ለገበያ ባቀረቡ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ከቀላል እስከ ከባድ ርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
ህዝቡን ለምርት እጥረት ለመዳረግ ብሎም የዋጋ ንረትን ለመጨመር የተንቀሳቀሱ 380 የሚሆኑ ነጋዴዎች ምርት ደብቀው የተገኙ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በነጋዴዎቹ ላይ ርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
ከ26 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ የዋጋ ዝርዝር ያልለጠፉ፣ ያለ አድራሻ የነገዱ እና መሰል ችግር የታየባቸው ነጋዴዎች መሆናቸውን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ከህዝብ ጤንነት ይልቅ ያለአግባብ መበልፀግ እና ማደግ የጣሩ 1 ሺህ 169 ህገወጥ ነጋዴዎች ምርትን ከባእድ ነገር ጋር ቀላቅለው ለሽያጭ የቀረቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በነዚህ ነጋዴዎች ላይ አስፈላጊው የእርምት ርምጃ መወሰዱን አብራርተዋል።
በተጨማሪም 1 ሺህ 778 የሚሆኑ ነጋዴዎች ትክክለኛ ያልሆኑ መለኪያ መሳሪያዎችን በመጠቀም ህዝቡን ሲያጭበረብሩ እና ሲበዘብዙ ብሎም ላልተገባ የኑሮ ውድነት እየዳረጉ እንደተገኙና የማስተካከያ ርምጃ እንደተወሰደባቸው አብራርተዋል።
ንግድን ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ፣ ተደራሽ እና ፍትሀዊ ለማድረግ የግብይት እና የንግድ ስርዓቱ በቴክኖሎጂ መደገፍ አለበት በሚል ሰፊ ስራ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም የነዳጅ ሽያጭ፣ የንግድ ፈቃድና እድሳት፣ የገበያ መረጃ እና የምርት ትስስር ሂደቱን በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ 352 ሺህ ነጋዴዎች የሚገኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከነዚህ ውስጥ ንግድ ፈቃድን ባወጡበት ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በ278 ሺህ ነጋዴዎች ላይ የበር ለበር ፍተሻ በማድረግ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ብለዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎችም ሆነ ህብረተሰቡ ህገወጥ የንግድ ስርአትን በማውገዝ ህጋዊ የንግድ ስርዓትን በማበረታታት የበኩሉን እገዛ ማድረግ አለበት በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
#ጋዜጣፕላስ
የደሞዝ ጭማሪን ሰበብ አድርገው ሕገወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ርምጃ እንደተወሰደባቸው የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከደሞዝ ጭማሪ ጋር ተያይዞ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ንረት እና ቀጣይ ርምጃዎችን አስመለክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም ሙሀመድ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የደሞዝ ጭማሪን ተከትሎ የሚመጣን የዋጋ ንረት ለመከላከል የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ተጠናክረዋል።
በዚህም የደመወዝ መጨመርን እንደ ሰበብ በመጠቀም የዋጋ ንረት እንዲመጣ ባደረጉ ነጋዴዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ ርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
በተደረገ የክትትል እና የቁጥጥር ስራም የደሞዝ ጭማሪን ሰበብ አድርገው ሕገወጥ ድርጊት ላይ የተሳተፉ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ርምጃ መወሰዱን አብራርተዋል።
ያለ አግባብ ዋጋ በጨመሩ፣ ምርት በደበቁ እና የምርት ጥራት አጓድለው ለገበያ ባቀረቡ ከ39 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ከቀላል እስከ ከባድ ርምጃ ተወስዷል ብለዋል።
ህዝቡን ለምርት እጥረት ለመዳረግ ብሎም የዋጋ ንረትን ለመጨመር የተንቀሳቀሱ 380 የሚሆኑ ነጋዴዎች ምርት ደብቀው የተገኙ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በነጋዴዎቹ ላይ ርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
ከ26 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ የዋጋ ዝርዝር ያልለጠፉ፣ ያለ አድራሻ የነገዱ እና መሰል ችግር የታየባቸው ነጋዴዎች መሆናቸውን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ ከህዝብ ጤንነት ይልቅ ያለአግባብ መበልፀግ እና ማደግ የጣሩ 1 ሺህ 169 ህገወጥ ነጋዴዎች ምርትን ከባእድ ነገር ጋር ቀላቅለው ለሽያጭ የቀረቡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በነዚህ ነጋዴዎች ላይ አስፈላጊው የእርምት ርምጃ መወሰዱን አብራርተዋል።
በተጨማሪም 1 ሺህ 778 የሚሆኑ ነጋዴዎች ትክክለኛ ያልሆኑ መለኪያ መሳሪያዎችን በመጠቀም ህዝቡን ሲያጭበረብሩ እና ሲበዘብዙ ብሎም ላልተገባ የኑሮ ውድነት እየዳረጉ እንደተገኙና የማስተካከያ ርምጃ እንደተወሰደባቸው አብራርተዋል።
ንግድን ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ፣ ተደራሽ እና ፍትሀዊ ለማድረግ የግብይት እና የንግድ ስርዓቱ በቴክኖሎጂ መደገፍ አለበት በሚል ሰፊ ስራ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም የነዳጅ ሽያጭ፣ የንግድ ፈቃድና እድሳት፣ የገበያ መረጃ እና የምርት ትስስር ሂደቱን በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ 352 ሺህ ነጋዴዎች የሚገኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከነዚህ ውስጥ ንግድ ፈቃድን ባወጡበት ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በ278 ሺህ ነጋዴዎች ላይ የበር ለበር ፍተሻ በማድረግ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ብለዋል።
ህጋዊ ነጋዴዎችም ሆነ ህብረተሰቡ ህገወጥ የንግድ ስርአትን በማውገዝ ህጋዊ የንግድ ስርዓትን በማበረታታት የበኩሉን እገዛ ማድረግ አለበት በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።
#ጋዜጣፕላስ
8 months ago
“የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የማግኘት ጉዳይ አይቀሬ ነው”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የማግኘት ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ገለፁ።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ ትናንት ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የማግኘት ጉዳይ አይቀሬ ነው ብለዋል።
ለብዙ ሀገራት በተናጠል በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ለጉዳዩም ቅድሚያ የሚሰጠው ሰላምና ንግግር ስለሆነ በንግግር መፍትሔ እንዲመጣ ጠይቀዋል።
የኤርትራ ህዝብ አሁንም ወንድም ህዝብ ነው፤ ሀገሩን ለቅቆ እየተሰደደ ያለ ህዝብ ነው ከዚህ ህዝብ ጋር በጋራ መሥራት ፍላጎታችን ነው፤ በፍጹም የውጊያ መሻት የለንም ብለዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ የተነሳው የውስጥ ጉዳዩን ለመሸፈን ነው ተብሎ የተነሳው ትክክል እንዳልሆነ፤ የሚሸፍን የውስጥ ጉዳይም እንደሌለ፤ ያለው ልማት መሆኑን አመልክተዋል።
#ጋዜጣፕላስ
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የማግኘት ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ገለፁ።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ ትናንት ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ ቀይ ባህርን የማግኘት ጉዳይ አይቀሬ ነው ብለዋል።
ለብዙ ሀገራት በተናጠል በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ለጉዳዩም ቅድሚያ የሚሰጠው ሰላምና ንግግር ስለሆነ በንግግር መፍትሔ እንዲመጣ ጠይቀዋል።
የኤርትራ ህዝብ አሁንም ወንድም ህዝብ ነው፤ ሀገሩን ለቅቆ እየተሰደደ ያለ ህዝብ ነው ከዚህ ህዝብ ጋር በጋራ መሥራት ፍላጎታችን ነው፤ በፍጹም የውጊያ መሻት የለንም ብለዋል።
የቀይ ባህር ጉዳይ የተነሳው የውስጥ ጉዳዩን ለመሸፈን ነው ተብሎ የተነሳው ትክክል እንዳልሆነ፤ የሚሸፍን የውስጥ ጉዳይም እንደሌለ፤ ያለው ልማት መሆኑን አመልክተዋል።
#ጋዜጣፕላስ
8 months ago
ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ አደረገች
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን አስታወቀች።
ሀገሪቱ ያደረገችው የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ እራሷን የመከላከል ቴክኒካል አቅሟን እያሳደገች ስለመሆኑ ግልጽ ማስረጃ መሆኑን አረጋግጣለች።
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮሪያ በሚሳኤል አስተዳደር የተካሄደውን ሙከራ፣ የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሃፊ ፓክ ጆንግ ቾን፣ የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ጃንግ ቻንግ ሃ መምራታቸውን የኮሪያ ማዕከላዊ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
አዲሱ የጦር መሣሪያ ስርዓት ከጠላት ሊሰነዘሩ የሚችሉ ስትራቴጂካዊ ጥቃቶችን በዘላቂነት እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመመከት እንደሚያስችል ተነግሯል።
የፒዮንግያንግ እንቅስቃሴ ጦርነትን ቀድሞ ለማስቀረት ያለመና ዓላማው ራስን መከላከል ብቻ መሆኑን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል።
የደቡብ ኮሪያ ጦር ፒዮንግያንግ በርካታ የአጭር ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ምስራቅ ባህር መተኮሷን አስታውቋል።
አሜሪካ ሙከራው ህገ-ወጥ እና የቀጠናውን መረጋጋት የሚረብሽ ነው በማለት ያወገዘች ሲሆን፤ ሰሜን ኮሪያ የተለያዩ የሰላም ስምምነቶችን ከሚጥሱ ተጨማሪ ድርጊቶች እንዲትተቀብ ጠይቃለች።
በክብረአብ በላቸው #ጋዜጣፕላስ #ዓለምዓቀፍ #ሰሜንኮሪያ #ደቡብኮሪያ
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ የተሳካ የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን አስታወቀች።
ሀገሪቱ ያደረገችው የሃይፐርሶኒክ ሚሳኤል ሙከራ እራሷን የመከላከል ቴክኒካል አቅሟን እያሳደገች ስለመሆኑ ግልጽ ማስረጃ መሆኑን አረጋግጣለች።
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮሪያ በሚሳኤል አስተዳደር የተካሄደውን ሙከራ፣ የኮሪያ የሰራተኞች ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፀሃፊ ፓክ ጆንግ ቾን፣ የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ጃንግ ቻንግ ሃ መምራታቸውን የኮሪያ ማዕከላዊ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
አዲሱ የጦር መሣሪያ ስርዓት ከጠላት ሊሰነዘሩ የሚችሉ ስትራቴጂካዊ ጥቃቶችን በዘላቂነት እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመመከት እንደሚያስችል ተነግሯል።
የፒዮንግያንግ እንቅስቃሴ ጦርነትን ቀድሞ ለማስቀረት ያለመና ዓላማው ራስን መከላከል ብቻ መሆኑን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል።
የደቡብ ኮሪያ ጦር ፒዮንግያንግ በርካታ የአጭር ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎችን ወደ ምስራቅ ባህር መተኮሷን አስታውቋል።
አሜሪካ ሙከራው ህገ-ወጥ እና የቀጠናውን መረጋጋት የሚረብሽ ነው በማለት ያወገዘች ሲሆን፤ ሰሜን ኮሪያ የተለያዩ የሰላም ስምምነቶችን ከሚጥሱ ተጨማሪ ድርጊቶች እንዲትተቀብ ጠይቃለች።
በክብረአብ በላቸው #ጋዜጣፕላስ #ዓለምዓቀፍ #ሰሜንኮሪያ #ደቡብኮሪያ
Comments