Logo
SeledaPost
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ ሊደርስበት ተቃርቦ እንደነበር ተዘገበ

በህንድ የኢንዲራ ጋንዲ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ላይ ባለው ከባድ የሥራ ጫና ምክንያት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የቪስታራ አየር መንገድ አውሮፕላኖች በኅዳር 10 ቀን 2023 አደጋ ሊደርስባቸው ተቃርቦ እንደነበር የአውሮፕላን አደጋ ምርመራ ቢሮ ባወጣው የመጨረሻ ዘገባ ላይ አስታወቀ።

አንድ የ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 787 አውሮፕላን ሊነሳ ሲዘጋጅ፣ ከጎኑ የ ቪስታራ አየር መንገድ አውሮፕላን ለማረፍ እየተቃረበ ነበር።

በከፍተኛ ነፋስ ምክንያት የቪስታራ አውሮፕላን የማረፍ ሙከራውን ሲያቋርጥ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጋር ሊጋጭ ተቃርቦ እንደነበር መገለጹን ካፒታል ዘግቧል።

seledadotio
seledadotio
11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.