በአዲስ አበባ በአዲስ ዓመት ባልና ሚስት በከሰል ጭስ ታፍነው መሞታቸው ተነገረ
በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ አመት ዋዜማ እና በእለቱ በትራፊክም አደጋ የሞተሰው አለመኖሩን እና የወንጀል አደጋ አለመድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ የተናገሩ ሲሆን ከወንጀል ውጭ በከሰል ጭስ መታፈን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።
በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7ጣፎ ኮዲሚኒየም እድሜቸው 75 አመት አዛውንት ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አመት ዋዜማ ምሽት በከሰል ጭስ ታፍነው ህይወታቸው አልፏል። በተመሳሳይ በለሚኩራ ክፍለከተማ ወረዳ 13 ህዳሴ ትምህርት ቤት ጀርባ በአዲስ አመት መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 6 ሰአት ባለትዳሮች በከሰል ጭስ ታፍነው ሞተው መገኘታቸውን ኮማንደር ማርቆስ ተናግረዋል።
ባለትዳሮቹ እሱ የ35 አመት ወጣት የትዳር አጋሩም ደግሞ የ27 አመት ወጣት መሆናን ፖሊስ የገለፀ ሲሆን በከሰል ጭሱ ሁለቱም ሞተው መገኘታቸውን ተነግሯል።
በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ አመት ዋዜማ እና በእለቱ በትራፊክም አደጋ የሞተሰው አለመኖሩን እና የወንጀል አደጋ አለመድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ የተናገሩ ሲሆን ከወንጀል ውጭ በከሰል ጭስ መታፈን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።
በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7ጣፎ ኮዲሚኒየም እድሜቸው 75 አመት አዛውንት ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አመት ዋዜማ ምሽት በከሰል ጭስ ታፍነው ህይወታቸው አልፏል። በተመሳሳይ በለሚኩራ ክፍለከተማ ወረዳ 13 ህዳሴ ትምህርት ቤት ጀርባ በአዲስ አመት መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 6 ሰአት ባለትዳሮች በከሰል ጭስ ታፍነው ሞተው መገኘታቸውን ኮማንደር ማርቆስ ተናግረዋል።
ባለትዳሮቹ እሱ የ35 አመት ወጣት የትዳር አጋሩም ደግሞ የ27 አመት ወጣት መሆናን ፖሊስ የገለፀ ሲሆን በከሰል ጭሱ ሁለቱም ሞተው መገኘታቸውን ተነግሯል።
11 months ago