Logo
Getu Temesgen
በአራት ወራቶች የተጠናቀቁት የጋር መኖሪያ ቤቶች በአዳማ
#ethiopia | በአዳማ ከተማ ጂ+5 27 ብሎክ የጋራ መኖርያ ቤቶች በዘመናዊ መልኩ በአራት ወራት ውስጥ ተገንብተው ተጠናቀው ተመርቀዋል።

በአዳማ ከተማ አንዶዴ መንደር ተገንብተው በዛሬው ዕለት የተመረቁት የጋራ መኖሪያ ቤት ሕንፃዎች በውስጣቸው 815 የመኖሪያ ክፍሎችን መያዛቸው የተገለፀ ሲሆን የሚ'ሰጡትም በልማት ምክንያት ከከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች ከመኖሪያቸው ለተነሱ ነዋሪዎች መሆኑ ተገልጿል።

አራት ወራትን እንደፈጀ በተገለጸው በዚሁ የግንባታ ሥራ ሂደት ከሦስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር መ'ቻሉን የአዳማ ከተማ ከንቲባ ኃይሉ ጀልዴ ተናግረዋል።

ከተማዋን ወደ ስማርት ሲቲነት ለመለወጥ እየተሠራ መሆኑም በዚሁ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገለፀ ሲሆን የዛሬው የመኖሪያ መንደር ግንባታም የዚሁ ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው ተብሏል።

ሷሊህ መሐመድ
ከአዳማ

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.