Logo
SeledaPost
በወላይታ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ

በወላይታ ዞን ዱጉና ፋንጎ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

ከኮንሶ ወደ ሞጆ በሬ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኤፍኤስአር የጭነት ተሽከርካሪ የመገልበጥ አደጋ እንደደረሰበት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ም/ል ኮማንደር ኤሊያስ ሜንታ  ተናግረዋል፡፡

አደጋው የደረሰው በወረዳው ፋንጎ ኮይሻ ቀበሌ ሌሊት 7፡30 ገደማ ሲሆን፥ የአሽከርካሪውና የረዳቱ ህይወት ወዲያው አልፏል፡፡

በተሽከርካሪው ላይ ተጭነው የነበሩ 17 በሬዎች በሙሉ መሞታቸውን ገልጸው፥ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ነው ም/ል ኮማንደር ኤሊያስ የገለጹት።

Seledadotio
Seledadotio
9 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.