Logo
FIDEL POST NEWS
በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ለሁለተኛ ተከታታይ ሳምንት ወረደ

ነዳጅ አምራች ሀገራት (ኦፔክ) እና አጋሮቻቸው ምርታቸውን ስለሚጨምሩ በሚቀጥለው ዓመት የፍላጎት መጠንን በእጅጉ የሚበልጥ አቅርቦት ይኖራል የሚል ስጋት በነጋዴዎች ዘንድ በመፈጠሩ የነዳጅ ዋጋ በዓለም ገበያ ለሁለተኛ ተከታታይ ሳምንት ወርዷል።

በለንደን ገበያ የአንድ በርሜል ዋጋ ባለፈው ሳምንት በ1.1 በመቶ ቀንሶ ወደ 65.85 ዶላር ሲደርስ፣ በአሜሪካ ገበያ ደግሞ የአንድ በርሜል ዋጋ በ1.7 በመቶ ቀንሶ 62.80 ዶላር ሆኗል።
የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ እና የነዳጅ ላኪ ሀገራት ድርጅት (ኦፔክ) እና አጋሮቹ ምርታቸውን እንደሚያሳድጉ ማስታወቃቸውን ተከትሎ፣ ዓለም አቀፉ የኃይል ኤጀንሲ (IEA) ገበያው በሚቀጥለው ዓመት የምርት ፍላጎትን የሚበልጥ ከፍተኛ አቅርቦት እንደሚያስመዘግብ አስታውቋል።

ኤጀንሲው በቅርብ ጊዜ በሰጠው ትንበያ እስከ 2025 ድረስ የነዳጅ አቅርቦት ግምቱን ያሳደገ ሲሆን፣ የዘንድሮው የነዳጅ አቅርቦት ከፍላጎት ከሶስት እጥፍ በላይ በፍጥነት እንደሚያድግ ይጠበቃል። ኤጀንሲው የነዳጅ አቅርቦት በ2025 በቀን በ2.5 ሚሊዮን በርሜል እንደሚያድግ የሚጠብቅ ሲሆን፣ ይህም ከቀደመው በ2.1 ሚሊዮን በርሜል ይጨምራል ከሚለው ግምት በላይ ነው።

በተመሳሳይ ጊዜ የዘንድሮውን ዓለም አቀፍ የነዳጅ ፍላጎት ዕድገት ትንበያ በጥቂቱ የቀነሰ ሲሆን፣ አሁን የፍላጎት ዕድገት በቀን 680,000 በርሜል ብቻ እንደሚደርስ ይጠበቃል። ነጋዴዎች በአሜሪካ ያለው የቀዘቀዘ ፍላጎትም አሳስቧቸዋል።

ከአሜሪካን ፔትሮሊየም ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በአሜሪካ የሚገኘው የድፍድፍ ነዳጅ ክምችት ከሁለት ሳምንት በፊት በ1.5 ሚሊዮን በርሜል ጨምሯል።
12 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.