Logo
FastMereja
ክቡር ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ እና በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያስተማራቸውን 72 ተማሪዎች በደማቅ ሥነሥርዓት አስመረቀ።

ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ ኩሪፍቱ ሪዞርት አፍሪካን ቪሌጅ በተሰናዳው ደማቅ ስነ-ስርዓት ያስመረቀ ሲሆን በዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት የአፍሪካ ቢዝነስ ስኩል ማህበር ዳይሬክተር ላና ኤልራምሊ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንዲሁም በዕለቱ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች ሜዳሊያና የዋንጫ ሸልማት ተበርክቷል።

ክቡር ኮሌጅ በ2013 ዓ ም ዕውቅና አግኝቶ የተመሰረተ የአፍሪካ ቢዝነስ ስኩል ማህበር አባል እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው።

1 year ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.