Logo
Getu Temesgen
የዩክሬን ፓርላማ ዩሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ ሾመ
#ethiopia | የዩክሬን ፓርላማ የዩሊያ ስቪሪደንኮ የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በማድረግ በ262 ድምጽ አጽድቋል።

ስቪሪደንኮ ከህዳር 2021 ጀምሮ የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

የዩክሬንን ኢኮኖሚና ማህበራዊ አቅም ማጠናከር፤ የዩክሬናውያንን የድጋፍ ፕሮግራሞችን ማስፋፋትና የሀገር ውስጥ የጦር መሳሪያ ምርትን ማስፋፋት የመንግስታቸው ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።

የዩክሬን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የተረከበች ሁለተኛዋ ሴት መሆኗን አናዶሉ ዘግቧል፡፡ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ስቪሪደንኮን በእጩነት ማቅረባቸውን ይታወሳል። #gazette_plus

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.