የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በበጀት ዓመቱ ከ34 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ
#ethiopia | አገልግሎት ከክልል መዝጋቢ እና ባለድርሻ አካላት ጋር የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት እቅድ የሴክተር ጉባኤ እያካሄደ ነው።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተው ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በወቅቱ እንደገለፁት፤ አገለግሎቱ የጉዞ ሰነዶችን በማዘጋጀት ከ100 ዓመት በላይ ቢያልፈውም ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ሰፊ ክፍተቶች ነበሩበት።
የአገልግሎቱ አሰራር የማህበረሰቡን ፍላጎት ያላሟላና ተገልጋዮችን ለእንግልትና ላልተፈለገ ወጪ ሲዳርግ የቆየ ነበር ብለዋል።
በጠጨማሪም በአገልግሎቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች እርካታ ያልበረባቸው ነበሩ ያሉት ዳይሬክተሯ በዚህም በ2016 ዓም 11 የሪፎርም አጀምዳዎች ተቀርጸው ወደ ስራ ገብተዋል ነው ያሉት።
ሪፎርሙ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያደርግ ሲሆን በዚህም የኤክትሮኒክስ ፓስፖርት ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አብራርተዋል።
ሪፎርሙ በዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ክፍተቶችን ከመቅረፍ ባሻገር አገልግሎት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዲያገኝ አድርጓል ብለው በዚህም በ2017 ዓ.ም ከዘርፉ ከ34 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የነበረውን የሰው ሃይል እጥረት እንዲሁም የደንበኞችን እርካታ በሚታይ ሁኔታ መቀየር ተችሏል ብለዋል።
#gazette_plus
#ethiopia | አገልግሎት ከክልል መዝጋቢ እና ባለድርሻ አካላት ጋር የ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት እቅድ የሴክተር ጉባኤ እያካሄደ ነው።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተው ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በወቅቱ እንደገለፁት፤ አገለግሎቱ የጉዞ ሰነዶችን በማዘጋጀት ከ100 ዓመት በላይ ቢያልፈውም ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ሰፊ ክፍተቶች ነበሩበት።
የአገልግሎቱ አሰራር የማህበረሰቡን ፍላጎት ያላሟላና ተገልጋዮችን ለእንግልትና ላልተፈለገ ወጪ ሲዳርግ የቆየ ነበር ብለዋል።
በጠጨማሪም በአገልግሎቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች እርካታ ያልበረባቸው ነበሩ ያሉት ዳይሬክተሯ በዚህም በ2016 ዓም 11 የሪፎርም አጀምዳዎች ተቀርጸው ወደ ስራ ገብተዋል ነው ያሉት።
ሪፎርሙ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዘመኑን የዋጀ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያደርግ ሲሆን በዚህም የኤክትሮኒክስ ፓስፖርት ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አብራርተዋል።
ሪፎርሙ በዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ክፍተቶችን ከመቅረፍ ባሻገር አገልግሎት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዲያገኝ አድርጓል ብለው በዚህም በ2017 ዓ.ም ከዘርፉ ከ34 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የነበረውን የሰው ሃይል እጥረት እንዲሁም የደንበኞችን እርካታ በሚታይ ሁኔታ መቀየር ተችሏል ብለዋል።
#gazette_plus
11 months ago