Logo
Getu Temesgen
የሁለተኛው የዓለም ጦርነት አርበኛ በ110 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | የብሪታንያ አንጋፋው የሁለተኛው የዓለም ጦርነት አርበኛ ዶናልድ ሮዝ በ110 ዓመታቸው አረፉ።

ሮዝ 1944 በኖርማንዲ የባህር ዳርቻ ላይ በተደረገው የዲ-ዴይ ማረፊያ ላይ የተሳተፉ ሲሆን፣ በሰሜን ጀርመን የሚገኘውን የበርገን-ቤልሰን ማጎሪያ ካምፕን ነጻ ባደረገው ክፍል ውስጥ ነበሩ።

በሰሜን እንግሊዝ የኤረዋሽ ቦሮው ካውንስል መሪ የሆኑት ጄምስ ዳውሰን የሮዝን ሞት ሲያስታውቁ “የጦርነት ጀግና” ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

“ኤረዋሽ እንደዚህ አይነት ነዋሪ በማግኘቷ ትልቅ ክብር ይሰማታል” ሲሉም አክለዋል።

ሮዝ የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ በ1914 የተወለዱት ነው የተወለዱት።

ከለንደን በስተደቡብ ምዕራብ ከምትገኘው የዌስትኮት መንደር የመጡት ሮዝ፣ በ23 ዓመታቸው ጦር ሠራዊቱን ተቀላቅለው በሰሜን አፍሪካ፣ ጣሊያንና ፈረንሳይ አገልግለዋል።

በርካታ ሜዳሊያዎችን የተቀበሉ ሲሆን የፈረንሳይ ከፍተኛ ሽልማት የሆነው ሌጌዎን ዲ’ኦኑር (Legion d’Honneur) ተሸልመዋል። #gazette_plus

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.