Logo
Getu Temesgen
ሁቲዎች ሁለተኛዋን የጭነት መርከብ በቀይ ባህር አሰመጡ
#ethiopia | የየመን ሁቲዎች በጭነት መርከብ ላይ ባደረሱት ጥቃት በቀይ ባህር አሰመጡ።

በጥቃቱም በትንሹ ሶስት ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታውቋል።

25 ሠራተኞችን የጫነው ኢተርኒቲ ሲ ከትናንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ ሮኬቶች እና በእጅ ቦምቦችን በመመታቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል ሲል የእንግሊዝ የባህር ንግድ ኦፕሬሽን ኤጀንሲ ገልጿል።

በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት ሁቲዎች ኢተርኒቲ ሲን ያጠቁት ወደ እስራኤል በማምራት ላይ እያለ ሲሆን፤ ቁጥራቸው ያልተገለጸ ሠራተኞችን ወደ "ድብቅ ቦታ" መውሰዳቸውም ተመላክቷል።

በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች ብዙ በህይወት የተረፉ ሠራተኞችን ማገታቸውን ገልጾ፤ የታገቱት ሠራተኞች በአስቸኳይ እንዲፈቱም ጠይቋል።

ከህዳር 2023 ጀምሮ ሁቲዎች በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ ላይ በሚሳኤል፣ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና በትንንሽ ጀልባዎች ጥቃት ወደ 70 የሚጠጉ የንግድ መርከቦችን ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል። #gazette_plus

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.