Logo
Getu Temesgen
"የኢኮኖሚና የቢዝነስ ዘገባ አዘጋጆች ግልጽና ቀላል ቋንቋን መጠቀም ይጠበቅባቸዋል"

- ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር)
#ethiopia | የኢኮኖሚና የቢዝነስ ዘገባ አዘጋጆች ግልጽና ቀላል ቋንቋን መጠቀም ይጠበቅባቸዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) ገለጹ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር)፤ የዘመን ኢኮኖሚ መጽሄት የይዘትና የቅርጽ ሙያዊ ቅኝት አቅርበዋል።

ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ አብዛኞቹ የኢኮኖሚ እና የቢዝነስ ዘገባዎች ቁጥር፣ ሙያዊና ከባድ ቃላት የሚበዛባቸው ናቸው።

የኢኮኖሚ እና የቢዝነስ ሪፖርተሮች ቀላል እና ግልጽ ቋንቋ መጠቀም እና ቁጥርን ወደቃላት ቀይረው ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

ዘመን ኢኮኖሚን መጽሄት በሚመለከት የሚቀርቡት ጹሁፎች ወቅታዊ መሆን፣ መረጃዎች ተተንትነው መቅረባቸው፣ የምንጭ አጠቃቀም፣ የማህበረሰቡን ጉዳይ ሽፋን መሰጠት፣ የፎቶ ግራፍና የዲዛይን አጠቃቀም፣ የአምድ ስብጥር ጠንካራ ጎኖች መሆናቸውን ተናግረዋል።
#gazette_plus

12 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.