ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ አስገባ
#ethiopia | የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በማዕድን ዘርፍ እያስመዘገበ ያለውን አስደናቂ ስኬት በመቀጠል በ2018 በጀት ዓመት እስከ ሰኔ ወር ድረስ 8 ሺህ 985 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉን የክልሉ ማዕድን ቢሮ አስታውቋል።
ይህ አስደናቂ ውጤት በ2017 በጀት ዓመት ገቢ ከተደረገው 4 ሺህ 779 ነጥብ 71 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ጋር ሲነጻጸር የ4 ሺህ 205 ኪሎ ግራም ታላቅ ብልጫ ያለው ሲሆን የክልሉን የወርቅ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን አመላካች ሆኗል።
በሀገር ደረጃ ከወርቅ ማዕድን ኤክስፖርት ከተገኘው 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ውስጥ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ድርሻ 1 ነጥብ 18 ቢሊዮን ዶላር ወይም 21 ነጥብ 44 በመቶ መሆኑ ደግሞ ክልሉ ለሀገር ኢኮኖሚ እያበረከተ ያለውን ወሳኝ ሚና በግልጽ ያሳያል።
ይሁን እንጂ በክልሉ በስፋት የሚስተዋለው ባሕላዊ የወርቅ አመራረት ዘዴ አሁንም ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ምክንያት እየሆነ እንደሚገኝ የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በጋዜጣ ፕላስ ዘገባ መሠረት ወርቁ በአግባቡ ሳይጠራ ከተረፈ ምርት ጋር አብሮ የሚወገድበትን ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ፣ አሁን ላይ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው።
ይህንን ውድ የተፈጥሮ ሀብት በዘመነ መንገድ በማምረት ማኅበረሰቡም ሆነ መንግሥት ከዘርፉ የሚገባቸውን ያህል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል እንደ ቤጉ-ሚድሮክ ካሉ የግል ፕሮጀክቶች ጋር በቅንጅት መሥራት ለቀጣዩ ምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በማዕድን ዘርፍ እያስመዘገበ ያለውን አስደናቂ ስኬት በመቀጠል በ2018 በጀት ዓመት እስከ ሰኔ ወር ድረስ 8 ሺህ 985 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉን የክልሉ ማዕድን ቢሮ አስታውቋል።
ይህ አስደናቂ ውጤት በ2017 በጀት ዓመት ገቢ ከተደረገው 4 ሺህ 779 ነጥብ 71 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ጋር ሲነጻጸር የ4 ሺህ 205 ኪሎ ግራም ታላቅ ብልጫ ያለው ሲሆን የክልሉን የወርቅ ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን አመላካች ሆኗል።
በሀገር ደረጃ ከወርቅ ማዕድን ኤክስፖርት ከተገኘው 5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ውስጥ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ድርሻ 1 ነጥብ 18 ቢሊዮን ዶላር ወይም 21 ነጥብ 44 በመቶ መሆኑ ደግሞ ክልሉ ለሀገር ኢኮኖሚ እያበረከተ ያለውን ወሳኝ ሚና በግልጽ ያሳያል።
ይሁን እንጂ በክልሉ በስፋት የሚስተዋለው ባሕላዊ የወርቅ አመራረት ዘዴ አሁንም ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ምክንያት እየሆነ እንደሚገኝ የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል።
በጋዜጣ ፕላስ ዘገባ መሠረት ወርቁ በአግባቡ ሳይጠራ ከተረፈ ምርት ጋር አብሮ የሚወገድበትን ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ፣ አሁን ላይ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው።
ይህንን ውድ የተፈጥሮ ሀብት በዘመነ መንገድ በማምረት ማኅበረሰቡም ሆነ መንግሥት ከዘርፉ የሚገባቸውን ያህል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል እንደ ቤጉ-ሚድሮክ ካሉ የግል ፕሮጀክቶች ጋር በቅንጅት መሥራት ለቀጣዩ ምርታማነት ዕድገት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
23 days ago