በሳውላ ከተማ የ8ተኛ ክፍል ፈተና ለሰው ሊፈተኑ የገቡ መምህርና ተማሪ በፖሊስ ተያዙ
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago