(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ለ28 ዓመታት ከዓለም ዋንጫው ታላቅ መድረክ ርቃ የቆየችው ስኮትላንድ... ከ36 ረጅም ዓመታት በኋላ የመጀመሪያዋን ታሪካዊ የዓለም ዋንጫ ድል ማጣጣም ችላለች። በቦስተን ስታዲየም በከፍተኛ የልብ ትርታ እና ጭንቀት ውስጥ ዛሬ ምሽት፣ ሃይቲን ጠባብ በሆነ ውጤት በማሸነፍ ስኮትላንድን ወደ ምድብ ሦስት አናት ላይ ያወጣው ጀግናው የአስቶንቪላው አምበል ጆን ማክጊን ነበር። ይህ ታሪካዊ ድል ስኮትላንድ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጥሎ ማለፉ ለመቀላቀል የምታደርገውን ጉዞ በከፍተኛ ተስፋ አብርቶታል።
የስኮትላንዱ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ስቲቭ ክላርክ ከጨዋታው በፊት እንደተናገሩት፣ በቅርቡ በተደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ላይ ድንቅ ብቃት ያሳየውን ራያን ክሪስቲን አስቀምጦ ጆን ማክጊንን በቋሚነት ማሰለፍ "በህይወቴ ከወሰንኳቸው ውሳኔዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ነበር" ብለው ነበር። ሆኖም የ31 ዓመቱ ማክጊን የአሰልጣኙን እምነት እና ድፍረት ወደ ሜዳ አውርዶ... በተግባር ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን በማስመስከር የሀገሩን ባለውለታነት ተወጥቷል።
ምንም እንኳን ስኮትላንዶች ጨዋታውን በንቃት ቢጀምሩም፣ ቀሪው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ግን ያሰቡትን ያህል አልጋ በአልጋ አልነበረም። ስኮትላንድ ኳስ በመቆጣጠር በኩል እጅግ ደካማ የነበረች ሲሆን፣ በተቃራኒው የካሪቢያኗ አገር ሃይቲ ወደ ግብ ክልል በርካታ አደገኛ ኳሶችን በማሻማት የፈጠረችው ጫና የስታዲየሙን ድባብ በጭንቀት አውጦት ነበር። በዚህም ምክንያት፣ በውድድሩ በዕድሜ አንጋፋ ከሆነው የ43 ዓመቱ ክሬግ ጎርደን ተመራጭ ሆኖ በቋሚነት የተሰለፈው ግብ ጠባቂው አንገስ ገን ከፍተኛ የትኩረት ፈተና ውስጥ ወድቆ አምሽቷል። ይህ የጭንቀት ስሜት በስኮትላንድ ደጋፊዎች አእምሮ ውስጥ ቀደም ሲል በኮስታሪካ፣ ኢራን እና ፔሩ ላይ የደረሱባቸውን ታሪካዊ ውድቀቶች ዳግም እንዲያስታውሱ አድርጓቸው ነበር።
በእርግጥ ጆን ማክጊን ጨዋታው ሊጠናቀቅ 20 ደቂቃዎች ሲቀሩት ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ ወደ ውጭ ቢሰድም፣ ቡድኑ እጅግ በፈለገው ወሳኝ ሰዓት ግን በውበት የታጀበ ባይሆንም እንኳ፣ "ሚትቦል" በሚለው ቅጽል ስሙ የሚጠራው ማክጊን ማሸነፊያዋን ወርቃማ ግብ አስቆጥሮ ለሀገሩ የድነት ብርሃን ሆኗል። በሌላ በኩል ጫና በበዛበት በዚህ ጨዋታ ላይ የቦርንማውዙ የመስመር አጥቂ ቤን ዶክ በቀኝ መስመር የሃይቲን ተከላካዮች ሲያምስ እና ሲፈትናቸው የነበረው አጓጊ ብቃት ሌላኛው የጨዋታው ድምቀት ነበር። ጨዋታው ገና ያለ ግብ እኩል በነበረበት ሰዓት ስኮት ማክቶሚናይ የመታው ኃይለኛ ኳስ የግቡን አግዳሚ ገጭቶ ሲመለስ፣ የፊት መስመር አጥቂዎቹ ቼ አዳምስ እና ላውረንስ ሻንክላንድ ግን በጨዋታው ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ ለማድረግ ተቸግረው ታይተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሃይቲዎች በኩል ፍራንትዝዲ ፒዬሮ በግንባሩ የገጨው እና ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣበት አደገኛ ሙከራ የስኮትላንድን ደጋፊዎች ልብ ያቆመ ክስተት ነበር።
"የተለየ" ሳምንት እያሳለፉ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኝ ክላርክ በውጤቱ እጅግ ቢደሰቱም.. ቡድናቸው በሜዳ ላይ ባሳየው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ግን ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። ምሽት ላይ 1 ለ 1 የተለያዩትን ብራዚልን እና ሞሮኮን በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያስተናግዱት ስኮትላንዶች፣ የፊታችን አርብ፣ ሰኔ 19 ወደ ቦስተን ተመልሰው ከሞሮኮ ጋር ከባድ ፍልሚያቸውን ያደርጋሉ። በቀጣይ ከሚያደርጓቸው ሁለት የምድብ ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ማሳካት ወደ ቀጣዩ ዙር እንደሚያሳልፋቸው ቢያውቁም፣ ይህ አሁን ያሳዩት ወላዋይ አቋም ግን ከታላላቆቹ ተጋጣሚዎቻቸው ጋር ቢገጥሙ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍላቸው እንደሚችል ተንታኞች አስጠንቅቀዋል።
የስኮትላንዱ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ስቲቭ ክላርክ ከጨዋታው በፊት እንደተናገሩት፣ በቅርቡ በተደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ላይ ድንቅ ብቃት ያሳየውን ራያን ክሪስቲን አስቀምጦ ጆን ማክጊንን በቋሚነት ማሰለፍ "በህይወቴ ከወሰንኳቸው ውሳኔዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ነበር" ብለው ነበር። ሆኖም የ31 ዓመቱ ማክጊን የአሰልጣኙን እምነት እና ድፍረት ወደ ሜዳ አውርዶ... በተግባር ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን በማስመስከር የሀገሩን ባለውለታነት ተወጥቷል።
ምንም እንኳን ስኮትላንዶች ጨዋታውን በንቃት ቢጀምሩም፣ ቀሪው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ግን ያሰቡትን ያህል አልጋ በአልጋ አልነበረም። ስኮትላንድ ኳስ በመቆጣጠር በኩል እጅግ ደካማ የነበረች ሲሆን፣ በተቃራኒው የካሪቢያኗ አገር ሃይቲ ወደ ግብ ክልል በርካታ አደገኛ ኳሶችን በማሻማት የፈጠረችው ጫና የስታዲየሙን ድባብ በጭንቀት አውጦት ነበር። በዚህም ምክንያት፣ በውድድሩ በዕድሜ አንጋፋ ከሆነው የ43 ዓመቱ ክሬግ ጎርደን ተመራጭ ሆኖ በቋሚነት የተሰለፈው ግብ ጠባቂው አንገስ ገን ከፍተኛ የትኩረት ፈተና ውስጥ ወድቆ አምሽቷል። ይህ የጭንቀት ስሜት በስኮትላንድ ደጋፊዎች አእምሮ ውስጥ ቀደም ሲል በኮስታሪካ፣ ኢራን እና ፔሩ ላይ የደረሱባቸውን ታሪካዊ ውድቀቶች ዳግም እንዲያስታውሱ አድርጓቸው ነበር።
በእርግጥ ጆን ማክጊን ጨዋታው ሊጠናቀቅ 20 ደቂቃዎች ሲቀሩት ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ ወደ ውጭ ቢሰድም፣ ቡድኑ እጅግ በፈለገው ወሳኝ ሰዓት ግን በውበት የታጀበ ባይሆንም እንኳ፣ "ሚትቦል" በሚለው ቅጽል ስሙ የሚጠራው ማክጊን ማሸነፊያዋን ወርቃማ ግብ አስቆጥሮ ለሀገሩ የድነት ብርሃን ሆኗል። በሌላ በኩል ጫና በበዛበት በዚህ ጨዋታ ላይ የቦርንማውዙ የመስመር አጥቂ ቤን ዶክ በቀኝ መስመር የሃይቲን ተከላካዮች ሲያምስ እና ሲፈትናቸው የነበረው አጓጊ ብቃት ሌላኛው የጨዋታው ድምቀት ነበር። ጨዋታው ገና ያለ ግብ እኩል በነበረበት ሰዓት ስኮት ማክቶሚናይ የመታው ኃይለኛ ኳስ የግቡን አግዳሚ ገጭቶ ሲመለስ፣ የፊት መስመር አጥቂዎቹ ቼ አዳምስ እና ላውረንስ ሻንክላንድ ግን በጨዋታው ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ ለማድረግ ተቸግረው ታይተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሃይቲዎች በኩል ፍራንትዝዲ ፒዬሮ በግንባሩ የገጨው እና ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣበት አደገኛ ሙከራ የስኮትላንድን ደጋፊዎች ልብ ያቆመ ክስተት ነበር።
"የተለየ" ሳምንት እያሳለፉ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኝ ክላርክ በውጤቱ እጅግ ቢደሰቱም.. ቡድናቸው በሜዳ ላይ ባሳየው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ግን ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። ምሽት ላይ 1 ለ 1 የተለያዩትን ብራዚልን እና ሞሮኮን በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያስተናግዱት ስኮትላንዶች፣ የፊታችን አርብ፣ ሰኔ 19 ወደ ቦስተን ተመልሰው ከሞሮኮ ጋር ከባድ ፍልሚያቸውን ያደርጋሉ። በቀጣይ ከሚያደርጓቸው ሁለት የምድብ ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ማሳካት ወደ ቀጣዩ ዙር እንደሚያሳልፋቸው ቢያውቁም፣ ይህ አሁን ያሳዩት ወላዋይ አቋም ግን ከታላላቆቹ ተጋጣሚዎቻቸው ጋር ቢገጥሙ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍላቸው እንደሚችል ተንታኞች አስጠንቅቀዋል።
9 hours ago