እስራኤል ሄዝቦላህ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንደምታጠናክር ኔታንያሁ ተናገሩ
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሄዝቦላህ ላይ የሚፈጸመው ጥቃት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን ተከትሎ የአገሪቱ ጦር በመላው ሊባኖስ አዲስ ዙር ጥቃት ማድረስ መጀመሩን አስታውቋል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በምስራቅ ሊባኖስ በሚገኘው ቤካ ሸለቆ እና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ላይ ጥቃት በመክፈት ሄዝቦላህን እየመታ መሆኑን ገልጿል።
ሄዝቦላህ በበኩሉ የእስራኤል ወታደሮች፣ ታንኮች፣ የጦር ሰፈሮች፣ ሕንፃዎች እና ሌሎች ስፍራዎችን ዒላማ ያደረጉ 22 የድሮን እና የሮኬት ጥቃቶችን በመፈጸም አጸፋውን መመለሱን አስታውቋል።
ሊባኖስ እና እስራኤል በዚህ ወር መጀመሪያ የደረሱበትን ተኩስ አቁም በ45 ቀናት ለማራዘም ስምምነት ቢፈጽሙም ውጊያው ቀጥሏል።
ኔታንያሁ ሰኞ ምሽት በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ እስራኤል “ከሄዝቦላህ ጋር ጦርነት ላይ” እንደሆነች ተናግረዋል። ሠራዊቱ “አድቃቂ ምት” እንዲፈጽም ማዘዛቸውንም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እስራኤል በከፈተችው ወታደራዊ ዘመቻ "ከ600 በላይ አሸባሪዎች” መገደላቸውንም ተናግረዋል። "አሁን ከእኛ የሚጠበቀው ጥቃቱን ማጠናከር እና ጥንካሬውን ይበልጥ መጨመር ነው" ሲሉም ተደምጠዋል።
ቤዛልል ስሞትሪች እና ኢታማር ቤን ግቪር የተባሉት ሁለት ቀኝ አክራሪ የእስራኤል ሚኒስትሮች ሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ የጦሩ ወታደራዊ ዘመቻ እንዲስፋፋ ጠይቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሄዝቦላህ ላይ የሚፈጸመው ጥቃት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን ተከትሎ የአገሪቱ ጦር በመላው ሊባኖስ አዲስ ዙር ጥቃት ማድረስ መጀመሩን አስታውቋል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በምስራቅ ሊባኖስ በሚገኘው ቤካ ሸለቆ እና በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ላይ ጥቃት በመክፈት ሄዝቦላህን እየመታ መሆኑን ገልጿል።
ሄዝቦላህ በበኩሉ የእስራኤል ወታደሮች፣ ታንኮች፣ የጦር ሰፈሮች፣ ሕንፃዎች እና ሌሎች ስፍራዎችን ዒላማ ያደረጉ 22 የድሮን እና የሮኬት ጥቃቶችን በመፈጸም አጸፋውን መመለሱን አስታውቋል።
ሊባኖስ እና እስራኤል በዚህ ወር መጀመሪያ የደረሱበትን ተኩስ አቁም በ45 ቀናት ለማራዘም ስምምነት ቢፈጽሙም ውጊያው ቀጥሏል።
ኔታንያሁ ሰኞ ምሽት በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ እስራኤል “ከሄዝቦላህ ጋር ጦርነት ላይ” እንደሆነች ተናግረዋል። ሠራዊቱ “አድቃቂ ምት” እንዲፈጽም ማዘዛቸውንም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እስራኤል በከፈተችው ወታደራዊ ዘመቻ "ከ600 በላይ አሸባሪዎች” መገደላቸውንም ተናግረዋል። "አሁን ከእኛ የሚጠበቀው ጥቃቱን ማጠናከር እና ጥንካሬውን ይበልጥ መጨመር ነው" ሲሉም ተደምጠዋል።
ቤዛልል ስሞትሪች እና ኢታማር ቤን ግቪር የተባሉት ሁለት ቀኝ አክራሪ የእስራኤል ሚኒስትሮች ሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ የጦሩ ወታደራዊ ዘመቻ እንዲስፋፋ ጠይቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago