Logo
FBC
ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ምክክር አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያስችል ምክክር በዋሽንግተን ዲሲ አካሂደዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የተመራውና የጠቅላይ ሚኒስትር ኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ፣ የብሄራዊ ደኀንነትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጀኔነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ያካተተ የልዑካን ቡድን ከአሜሪካ አቻዎቹ ጋር ተወያይቷል።

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ያካሄዱት የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክር በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን፤ ይኸውም የኢኮኖሚ ብልጽግናን፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና ጸጥታ እንዲሁም ቀጣናዊ ሰላም እና መረጋጋት ማስፈን የተመለከተ ነው።

የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ምክክሩ የሀገራቱን ግንኙነት ዘላቂ በሆነ መንገድ የሚያስቀጥል እና የሚያጠናክር መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.