Logo
Zehabesha
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ምክንያት፣ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የነዳጅ ገቢ እንዳጣች የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) ባለስልጣናትን ጠቅሶ 'አክሲዮስ' የዜና አውታር ዘገበ።

ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣናቱ እንደገለጹት፣ በእገዳው ወቅት ሁለት የነዳጅ ጫኝ መርከቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ 53 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ የጫኑ ሌሎች 31 መርከቦች በባህረ ሰላጤው ውስጥ መንቀሳቀስ ተስኗቸው ቆመዋል። በተጨማሪም አንዳንድ መርከቦች በአሜሪካ የባህር ኃይል ቁጥጥር ስር ላለመውደቅ በመስጋት፣ ነዳጃቸውን ወደ ቻይና ለማድረስ ረጅምና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ የጉዞ መስመር ለመጠቀም ተገደዋል።

አሜሪካ ይህንን እገዳ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችው፣ በእስራኤል፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚካሄደውን ጦርነት በዘላቂነት ለማስቆም በፓኪስታን አደራዳሪነት የቀረበውን የተኩስ አቁም ስምምነት ኢራን እንድትቀበል ጫና ለመፍጠር በማሰብ ነው።

ባለፈው ወር በእስራኤል እና በኢራን በሚደገፈው የሊባኖሱ ሄዝቦላህ መካከል የ10 ቀናት ጊዜያዊ የተኩስ አቁም መደረሱን ተከትሎ፣ ኢራን የሆርሙዝን ባህረ ሰላጤ ለንግድ መርከቦች ሙሉ በሙሉ ክፍት ማድረጓን አስታውቃ ነበር። ነገር ግን አሜሪካ ጦርነቱን በዘላቂነት የሚያቆም ስምምነት ላይ እስኪደረስ ድረስ እገዳዋን አላነሳም በማለቷ፣ ኢራንም በበኩሏ የሆርሙዝን መስመር ዳግም መዝጋቷን ዘገባው አስታውሷል።

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.