የአሜሪካ መንግስ በኢራቅ የሚገኙ ዜጎቹ በአስቸኳይ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ
#ethiopia | በኢራቅ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ከኢራን ጋር ግንኙነት ባላቸው ታጣቂዎች ሊሰነዘር የሚችል "ሰፋ ያለ" ጥቃት ስጋት መኖሩን ገልጾ፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲወጡ አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ የታጣቂዎቹ ኢላማ በሰሜን የሚገኘውን የኩርድ ክልል ጨምሮ በመላው ኢራቅ የሚገኙ አሜሪካውያን እና ከዋሽንግተን ጋር ግንኙነት ያላቸው ተቋማት ናቸው። በአሁኑ ወቅት በኢራቅ የአየር ክልል ውስጥ የሚሳኤል፣ የሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮን) እና የሮኬት ጥቃት ስጋት ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዜጎች በባግዳድ ወደሚገኘው ኤምባሲም ሆነ በኤርቢል ወደሚገኘው ቆንስላ ከመሄድ እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መግለጫው፤ የአየር ክልሉ ዝግ በመሆኑ ወደ ጎረቤት ሀገራት ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ቱርክ ለመሻገር የየብስ መስመሮችን እንዲጠቀሙ መክሯል።
በሌላ በኩል የመካከለኛው ምስራቅ ግጭቶች ተንታኝ የሆኑት ኤላጃህ ማግኒየር ለአልጀዚራ በሰጡት አስተያየት፣ በቀጠናው ያለው ጦርነት እንዲቆም ግልጽ የሆነ አሸናፊ መውጣት እንዳለበት ገልጸዋል። እንደ ተንታኙ ገለጻ እስካሁን የታዩት ግጭቶች እና የሰኔ 2025ቱ ክስተት ሁለቱም ወገኖች በሽንፈትም ሆነ በአሸናፊነት ያልወጡበት በመሆኑ፣ ዘላቂ የሰላም ድርድር ላይ መድረስ አልተቻለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #iraq #usa #securityalert #middleeastnews #iran #breakingnews #geopolitics #usmissioniraq
#ethiopia | በኢራቅ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ከኢራን ጋር ግንኙነት ባላቸው ታጣቂዎች ሊሰነዘር የሚችል "ሰፋ ያለ" ጥቃት ስጋት መኖሩን ገልጾ፣ በሀገሪቱ የሚገኙ የአሜሪካ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲወጡ አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ የታጣቂዎቹ ኢላማ በሰሜን የሚገኘውን የኩርድ ክልል ጨምሮ በመላው ኢራቅ የሚገኙ አሜሪካውያን እና ከዋሽንግተን ጋር ግንኙነት ያላቸው ተቋማት ናቸው። በአሁኑ ወቅት በኢራቅ የአየር ክልል ውስጥ የሚሳኤል፣ የሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮን) እና የሮኬት ጥቃት ስጋት ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዜጎች በባግዳድ ወደሚገኘው ኤምባሲም ሆነ በኤርቢል ወደሚገኘው ቆንስላ ከመሄድ እንዲቆጠቡ ያሳሰበው መግለጫው፤ የአየር ክልሉ ዝግ በመሆኑ ወደ ጎረቤት ሀገራት ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ቱርክ ለመሻገር የየብስ መስመሮችን እንዲጠቀሙ መክሯል።
በሌላ በኩል የመካከለኛው ምስራቅ ግጭቶች ተንታኝ የሆኑት ኤላጃህ ማግኒየር ለአልጀዚራ በሰጡት አስተያየት፣ በቀጠናው ያለው ጦርነት እንዲቆም ግልጽ የሆነ አሸናፊ መውጣት እንዳለበት ገልጸዋል። እንደ ተንታኙ ገለጻ እስካሁን የታዩት ግጭቶች እና የሰኔ 2025ቱ ክስተት ሁለቱም ወገኖች በሽንፈትም ሆነ በአሸናፊነት ያልወጡበት በመሆኑ፣ ዘላቂ የሰላም ድርድር ላይ መድረስ አልተቻለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #iraq #usa #securityalert #middleeastnews #iran #breakingnews #geopolitics #usmissioniraq
2 months ago