Logo
FastMereja
ሜታ የቲክቶክ እና የዩቲዩብ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችን ወደ ፌስቡክ ለመሳብ ወርሃዊ ክፍያ አቀረበ
#fastmereja I ​ሜታ የታወቁ የቪዲዮ ፈጣሪዎችን ከሌሎች ተቀናቃኝ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ወደ ፌስቡክ ለማምጣት "Creator Fast Track" የተሰኘ አዲስ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል። ኩባንያው ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የነበሯቸውን ቪዲዮዎች በፌስቡክ ላይ መልሰው እንዲለጥፉ በማድረግ ብቻ ወርሃዊ የገንዘብ ክፍያ እንደሚፈጽም አስታውቋል።

​የክፍያ ዝርዝር
የተመረጡ ፈጣሪዎች እንደ ተከታዮቻቸው ብዛት የሚከተለው ክፍያ ይቀርብላቸዋል፡
📌 ​100,000 ተከታዮች ያሏቸው፦ በወር $1,000።
📌 ​ከ1 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏቸው፦ በወር $3,000።
​📌 ከገንዘቡ ባሻገር፣ ፌስቡክ ለቪዲዮዎቹ ሰፊ ተደራሽነት (Boost) እንዲያገኙ ያደርጋል።

​ለመሳተፍ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች
​ፕሮግራሙ በአሁኑ ወቅት ጥብቅ መስፈርቶችን ያስቀመጠ ሲሆን፣ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡
📍በአሜሪካ ወይም በካናዳ የሚኖሩ እና ዕድሜያቸው 18 ዓመት የሞላቸው።
​📍በኢንስታግራም፣ ቲክቶክ ወይም ዩቲዩብ ቢያንስ 20,000 ተከታዮች ሊኖራቸው ይገባል።
​📍 ቢያንስ ለ30 ቀናት የቆየ የፌስቡክ ገጽ ያላቸው እና ባለፉት 6 ወራት ውስጥ ምንም ዓይነት "Reels" ያልለቀቁ።
​📍 ባለፉት 60 ቀናት ውስጥ ቢያንስ 30,000 የቪዲዮ እይታ ያላቸው።

​ይህ እርምጃ ሜታ በ2025 ለፈጣሪዎች የከፈለውን የክፍያ መጠን 3 ቢሊዮን ዶላር በማድረስ የ35 በመቶ ጭማሪ ካሳየ በኋላ የመጣ ነው። ሜታ በተለይ ቲክቶክ በአሜሪካ ውስጥ ካለበት የፖለቲካ ጫና እና የሕግ እገዳ ስጋት ጋር ተያይዞ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አማራጭ እንዲፈልጉ እያበረታታ ይገኛል።
#ሳይ_ቴክ

5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.