Logo
FastMereja
ድጋፋ ቀጥሏል !!!

በጋሞ ዞን በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ለተጎዱ ወገኖቻችን የ150,000 ሺህ ብር(አናያር ትሬዲንግ ,አግሮ ማይን , እሺ ሚዲያ እና ኮምኒኬሽን) የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።

​የድጋፍ ገንዘብ ርክክቡን ያከናወኑት ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳና ልዑካቸው ባስተላለፉት መልዕክትበአደጋው ምክንያት ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸው መጽናናትን ተመኝተዋል።

​ኢንስትራክተር ነፃነት ይህ ድጋፍ የመጀመሪያ ዙር መሆኑንና በቀጣይም አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

​ድጋፉን የተረከቡት የጋሞ አባቶችና የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በበኩላቸው፤ ተቋማቱ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላሳየው ወንድማዊ አጋርነትና ላደረጉት ድጋፍ በዞኑ ሕዝብና በመንግሥት ስም ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል ከጉዳቱ ክብደት የተነሳ ሌሎች ወገኖችም እገዛቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል ።

የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር CBE፦ 1000321312865

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.