Logo
FIDEL POST NEWS
ፈንጂ ወይስ ድርድር? በሆርሙዝ ሰርጥ እየመጣ ያለው ወታደራዊ ውጥረት

👉​የባህር ላይ ፈንጂዎች ስምሪት፦ የዩናይትድ ስቴትስ የስለላ ተቋማት ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የንግድ መርከቦች ማለፊያ መስመር ላይ የባህር ውስጥ ፈንጂዎችን (Naval Mines) ለማሰማራት እየተንቀሳቀሰች መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶችን ማየታቸውን CBS ዘግቧል።

👉​የአሰራር ዘዴ፦ ኢራን ፈንጂዎቹን ለማጓጓዝ አነስተኛ ጀልባዎችን እየተጠቀመች ሲሆን፣ እያንዳንዱ ጀልባ ከ2 እስከ 3 የሚደርሱ ፈንጂዎችን የመጫን አቅም እንዳለው Investing Live ጠቅሷል።

👉​የኢራን የፈንጂ ክምችት፦ ኢራን በክምችቷ ውስጥ ከ2,000 እስከ 6,000 የሚደርሱ የራሷ፣ የቻይና እና የሩሲያ ሰራሽ የባህር ውስጥ ፈንጂዎች እንዳሏት ይገመታል።

👉​የዶናልድ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ፈንጂዎቹን በአስቸኳይ እንድታነሳ ካልሆነ ግን "ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ" ወታደራዊ እርምጃ እንደሚጠብቃት በ TruthSocial ገጻቸው አስጠንቅቀዋል።

👉​የአሜሪካ የባህር ኃይል ሚና፦ የአሜሪካ የባህር ኃይል በወሽመጡ የሚያልፉ ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን ጥበቃ እንደሚያደርግ ትራምፕ የአስቸኳይ ጊዜ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

👉​የእስራኤል እና አሜሪካ ግንኙነት፦ አሜሪካ እስራኤል የኢራንን የኢነርጂ እና የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ የምታደርገውን ጥቃት እንድታቆም መጠየቋን Axios ዘግቧል።

​የነዳጅ ገበያ ስጋት፦ በዚህ ውጥረት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መዋዠቅ የታየ ሲሆን፣ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ (WTI) ዋጋ እስከ 87 ዶላር ደርሶ ነበር።

👉​የጎልድማን ሳክስ ግምት፦ ውጥረቱ ካልረገበ በ2026 አራተኛ ሩብ ዓመት የነዳጅ ዋጋ እንደ ሁኔታው አስከፊነት እስከ 93 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል።

👉​የዲፕሎማሲ ጥረት፦ የአሜሪካ ልዩ ተወካይ ዊትኮፍ (Vitkoff) ወደ እስራኤል በመጓዝ ኢራን ለንግግር ፈቃደኛ መሆኗንና የዲፕሎማሲ መፍትሄ የመኖሩን ሁኔታ እንደሚመረምሩ ተገልጿል።

👉​የኢራን አጸፋዊ ምላሽ፦ ኢራን በበኩሏ በባህረ ሰላጤው አካባቢ ለሚደረገው እገዳ ምላሽ በሚመስል መልኩ በዶናልድ ትራምፕ ላይ የዛቻ መልእክት ማስተላለፏ ተጠቅሷል።

​ምንጮች፦ CBS News, Axios, Investing Live, Goldman Sachs Internal Note እና የዶናልድ ትራምፕ ማህበራዊ ገጽ
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.