የሳዑዲ አረቢያ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
የሳዑዲ አረቢያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሊድ አብዱልከሪም አል ካሪጅ ከኤርራው ፕሬዚዳንት ጋር በአሥመራ ተገናኝተው መወያየታቸው ተገለፀ።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ከሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር የተገናኙት ሐሙስ የካቲት 5/2018 ዓ.ም. መሆኑን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስትር በይፋዊ የኤክስ ገጹ ላይ ይፋ አድርጓል።
የሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢንጂነር ማሌን ቢን አብዱልካሪም አል ካሬጂ እና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ሁለቱ አገራት ያላቸውን ወዳጅነት እና ትብብር ለማጠናከር መነጋገራው ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የሳዑዲ ልዑካን ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ጋር በቀጠናው እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል።
በዚህ ሳምንት አጋማሽ ላይ የሳዑዲ አረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በአዲስ አበባ በሁለትዮሽ እንዲሁም ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና የሳዑዲው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ውይይት በዝርዝር ባይገለጽም "በቁልፍ ዘርፎች ላይ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር" እንዲሁም "የሁለቱም አገራት ፍላጎት በሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መተባበር" ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሥልጣናት ወደ ሁለቱ አገራት ጉብኝት ያደረጉት ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዳግም ወፈደ ግጭት ይገባሉ የሚለው ስጋት ባየለበት ወቅት ነው።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት እና የሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው በቀይ ባሕር ዙሪያ የሚገኙ አገራት የቀጠናውን ሰላም እና ደኅንነት ዋስትና በማረጋገጥ ረገድ የሚኖራቸው ሚና ላይ መነጋራቸውን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ ልዑክ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ጋር “በቀይ ባሕር ዙሪያ የሚገኙ አገራት ተለዋዋጭ በሆነው ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች እና አዝማሚያዎች ባሻገር የአካባቢውን ሰላም እና ደኅንነት በማረጋገጥ ረገድ ስለሚኖራቸው አስተዋጽኦ ተነጋግረዋል።”
ሁለቱ አገራት በፖለቲካ፣ በምጣኔ ሀብት፣ በደኅንነት፣ በባህል እና በማኅበራዊ ዘርፎች ከዚህ ቀደም የደረሱባቸውን ሁለትዮሽ ስምምነቶች ተግባራዊ ለማድረግ መነጋገራቸው ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አወርቂ በታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማቅናት ከአልጋ ወራሽ ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማን ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ ባለፈው ሳምንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ተጉዘው ከልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።
ከሳዑዲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ጋር በተደረገው ውይይት "ሁለቱ አገራት የአፍሪካ ቀንድን ሰላም እና መረጋጋትን ለማስጠበቅ" በጋራ ለመሥራት እንደተስማሙ ተገልጿል።
BBC
የሳዑዲ አረቢያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሊድ አብዱልከሪም አል ካሪጅ ከኤርራው ፕሬዚዳንት ጋር በአሥመራ ተገናኝተው መወያየታቸው ተገለፀ።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ከሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር የተገናኙት ሐሙስ የካቲት 5/2018 ዓ.ም. መሆኑን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስትር በይፋዊ የኤክስ ገጹ ላይ ይፋ አድርጓል።
የሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢንጂነር ማሌን ቢን አብዱልካሪም አል ካሬጂ እና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ሁለቱ አገራት ያላቸውን ወዳጅነት እና ትብብር ለማጠናከር መነጋገራው ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የሳዑዲ ልዑካን ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ጋር በቀጠናው እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል።
በዚህ ሳምንት አጋማሽ ላይ የሳዑዲ አረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በአዲስ አበባ በሁለትዮሽ እንዲሁም ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና የሳዑዲው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ውይይት በዝርዝር ባይገለጽም "በቁልፍ ዘርፎች ላይ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር" እንዲሁም "የሁለቱም አገራት ፍላጎት በሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መተባበር" ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሥልጣናት ወደ ሁለቱ አገራት ጉብኝት ያደረጉት ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዳግም ወፈደ ግጭት ይገባሉ የሚለው ስጋት ባየለበት ወቅት ነው።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት እና የሳዑዲ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው በቀይ ባሕር ዙሪያ የሚገኙ አገራት የቀጠናውን ሰላም እና ደኅንነት ዋስትና በማረጋገጥ ረገድ የሚኖራቸው ሚና ላይ መነጋራቸውን የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ ልዑክ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ጋር “በቀይ ባሕር ዙሪያ የሚገኙ አገራት ተለዋዋጭ በሆነው ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች እና አዝማሚያዎች ባሻገር የአካባቢውን ሰላም እና ደኅንነት በማረጋገጥ ረገድ ስለሚኖራቸው አስተዋጽኦ ተነጋግረዋል።”
ሁለቱ አገራት በፖለቲካ፣ በምጣኔ ሀብት፣ በደኅንነት፣ በባህል እና በማኅበራዊ ዘርፎች ከዚህ ቀደም የደረሱባቸውን ሁለትዮሽ ስምምነቶች ተግባራዊ ለማድረግ መነጋገራቸው ተገልጿል።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አወርቂ በታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማቅናት ከአልጋ ወራሽ ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማን ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ ባለፈው ሳምንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ተጉዘው ከልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።
ከሳዑዲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሐን ጋር በተደረገው ውይይት "ሁለቱ አገራት የአፍሪካ ቀንድን ሰላም እና መረጋጋትን ለማስጠበቅ" በጋራ ለመሥራት እንደተስማሙ ተገልጿል።
BBC
6 months ago