Logo
Getu Temesgen
ያለደረሰኝ ሲገበያዩ የተገኙ 32 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
#ethiopia | ​ኦፕሬሽኑ በስጋ ቤቶች እና በግንባታ እቃዎች መሸጫዎች ላይ አነጣጥሯል

​የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ትላንት ቅዳሜ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ድንገተኛ ኦፕሬሽን፤ ህጋዊ ደረሰኝ ሳይቆርጡ ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ 32 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።

​የኦፕሬሽኑ ዝርዝር:
መርካቶን ጨምሮ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች በተደረገው በዚህ ዘመቻ፤ 19 ስጋ ቤቶች እና 6 የግንባታ እቃዎች መሸጫ ቤቶች ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሸ ግለሰቦቹ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

​እርምጃው:
በቁጥጥር ስር የዋሉት የንግድ ድርጅቱ ባለቤቶችና ሽያጭ ያከናወኑ ሰራተኞች ሲሆኑ፤ የመንግስትን ግብር ለመሰወር እና አዋጅን በመተላለፍ ወንጀል ተጠርጥረው ለፍርድ ይቀርባሉ።

​ማስጠንቀቂያ:
​የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኦፕሬሽን ተግባር በቀጣይ ቀናትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፤ ህብረተሰቡ ግብይት ሲፈጽም ደረሰኝ እንዲጠይቅ እና ጥቆማ ለመስጠት በ 7075 ነፃ የስልክ መስመር እንዲጠቀም ጥሪ አቅርቧል።

​ህግን ማክበር ለራስ ሰላም ነው!
​የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

​#addisababa #revenuesbureau #taxcompliance #operation #legalaction #mercato #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን

5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.