Logo
FIDEL POST NEWS
በአሜሪካ በ2026 የመጀመሪያው የሞት ቅጣት ተፈጸመ

​በአሜሪካ የቴክሳስ ግዛት የቀድሞ ፍቅረኛውን እና አዲስ ጓደኛዋን በመግደል የሞት ፍርድ ተፈርዶበት የነበረው የ55 ዓመቱ ቻርለስ ቪክቶር ቶምፕሰን፣ በ2026 በሀገሪቱ የሞት ቅጣት የተፈጸመበት የመጀመሪያው ሰው ሆኗል።
​📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦
​ወንጀሉ፦ እ.ኤ.አ. በሚያዚያ 1998 በሂዩስተን ከተማ የቀድሞ ፍቅረኛውን ግሌንዳ ዴኒስን እና አዲሱን ጓደኛዋን ዳረን ኬዝን በመኖሪያ ቤታቸው ገብቶ በጥይት በመግደሉ ነው።
​የቅጣት አፈጻጸሙ፦ ረቡዕ ምሽት 6፡50 ላይ በቴክሳስ የጥበቃ ማእከል በመርፌ መርዝ ተሰጥቶት ህይወቱ አልፏል።

​የመጨረሻ ቃላት፦ ቶምፕሰን ከመሞቱ በፊት ለተጎጂ ቤተሰቦች "ይቅርታ አድርጉልኝ" በማለት መልእክት አስተላልፏል። "በዚህ ሁኔታ ውስጥ አሸናፊ የለም፤ ቅጣቱ ከ28 ዓመታት በኋላም ቢሆን ተጨማሪ ሰዎችን የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ይከታል" ብሏል።

​ከእስር ቤት ማምለጡ፦ ቶምፕሰን እ.ኤ.አ. በ2005 የሞት ፍርድ በተፈረደበት ወቅት፣ የውሸት መታወቂያ በመጠቀም ከእስር ቤት አምልጦ ለሶስት ቀናት ተሰውሮ ከቆየ በኋላ በሉዊዚያና ተይዞ ነበር።

​💬 የቤተሰቦች ምላሽ
​የሟቹ የዳረን እናት ዴኒስ ኬን፣ የቶምፕሰን ሞት ከተረጋገጠ በኋላ ባጭሩ "እሱ አሁን ገሃነም ነው ያለው" በማለት ሀዘናቸውን ገልጸዋል።
6 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.