Logo
FIDEL POST NEWS
ግብፅ 3-1 ቤኒን

ግብፅ አነስተኛ ግምት ተሰጥቷት የነበረችውን ቤኒንን በተጨማሪ 30 ደቂቃ ባስቆጠረቻቸው ሁለት ግቦች በድምሩ 3-1 በማሸነፍ በአፍሪካ ዋንጫው ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች።

ቀድሞ ግብ ቢቆጠርባቸውም ​ቤኒኖች በመጀመሪያው 90 ደቂቃ ጠንካራ ተፎካካሪ ነበሩ።

በቤኒኑ ጆዴል ዶሱ አማካኝነት የአቻነት ግብ ተቆጥሮባቸው የነበረ ቢሆንም፣ ለግብፆች ማርዋን አቲያ አስደናቂ የመክፈቻ ግብ አስቆጥሮ ነበር።

በጭማሪ 30 ደቂቃ ላይ ሰባተኛው ደቂቃ ላይ በያሰር ኢብራሂም በጭንቅላት የተገጨች ግብ አማካኝነት ግብፆች ዳግም መሪነታቸውን አረጋግጠዋል።

​መሐመድ ሳላህ በጨዋታው መገባደጃ ሰከንዶች ተጨማሪ ግብ በማስቆጠር ሰባት ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ለሆነችው ግብፅ የ3 ለ 1 ድልን አቀናጅቷል።

ግብፅ በሩብ ፍጻሜው ከአይቮሪ ኮስት ወይም ከቡርኪና ፋሶ አሸናፊ ጋር ትጋጠማለች።
7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.