Logo
Getu Temesgen
የክብር የእራት ግብዣ

* "ስለ እናት ምድር" ፊልም አህጉራዊ ሽልማት
#ethiopia | 21ኛው የአፍሪካ የፊልም አካዳሚ ሽልማት (AMAA 2025) በናይጄሪያ ሌጎስ ተካሄዷል።

በሀገር ፍቅርና በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ያተኮረው "ስለ እናት ምድር" ፊልም የአፍሪካ የፊልም አካዳሚ ሽልማትን አግኝቷል።

ትኩረቱን በሀገር ፍቅርና በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ያደረገው እና በዳይሬክተር ቴዎድሮስ ተሾመ የተዘጋጀው "ስለ እናት ምድር" የተሰኘው ፊልም የዕይታ ጥበባት ውጤቶች (Visual Effects) ዘርፍ አሸንፏል።

ሽልማቱን የፊልሙ ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ተሾመ ተቀብሏል።

በአርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ በተዘጋጀው “ስለ እናት ምድር” ፊልም ላይ 30ሺ ሰዎች ተሳትፈውበታል።

መድረኩን የመራችው ታዋቂዋ ጋዜጠኛና አዘጋጅ ቪምባይ ሙቲንሂሪ እኛ በቀኝ ካልተገዛችው ኢትዮጵያ የምንማረው ብዙ ጉዳይ አለን ብላለች።

ኢትዮጵያውን በራሳቸው የውስጥ አቅም የገነቡት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የራሳቸውን የሃይል ፍላጎት ማሟላት ችለዋል ያለችው ቪምባይ የዚህ ዓይነቱ ተሞክሮ ለናይጄሪያ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሳ እንኳን ደስ ያላችሁ ብላለች፡፡

“ስለ እናት ምድር” ሽልማት ከተሰጠባቸው 26 ዘርፎች በስምንቱ እጩ ሆኖ ቀርቦ ነበር።

ይህንን አስመልክቶ ዛሬ በጎልደን ቱሊፕ ( ቦሌ መድኃኔዓለም) ከምሽቱ 12:00 ሰዓት የክብር የእራት ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።

የኪነጥበብ ቤተሰቦች በክብር ተጋብዛችኋል

AFRICA MOVIE ACADEMY AWARDS 2025

AAMA 2025 Award for Best Visual Effect

Winner:

Theodros Teshome

WWA ACHIEVEME VISLIAL EFFECH

You're Invited to a Special Celebration

The acclaimed Ethiopian filmmaker, for his outstanding achievement in winning the AAMA 2025 Award for Best Visual Effect This occasion also celebrates his exceptional contribution to the Ethiopian film industry, where his vision, dedication, and groundbreaking works have played a significant role in shaping and elevating Ethiopian cinema on the global stage.

Friends, celebrities, and distinguished guests will gather to mark this milestone, and your presence will be greatly appreciated.

December 18 at 6:00 PM

Golden Tulip Hotel, Bole Medhanialem

6 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.