በኮንጎ 31 ሰዎች በኢቦላ ሞቱ
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢቦላ ወረርሽኝ 31 ሰዎች መሞታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ በዚህ ወር ውስጥ ብቻ 48 ሰዎች በኢቦላ ተይዘዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት አስፈላጊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን በማድረስ፣ ባለሙያዎችን በማሰማራትና የኢቦላ ህክምና ማዕከል በማቋቋም ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ገልጸዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀው በሽታው ቀደም ሲል በሁለት ወረዳዎች ተከስቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ወደ አራት ወረዳዎች ተዛምቷል።
ወረርሽኙ ከሶስት ዓመታት በኋላ የታወጀው ከሁለት ሳምንት በፊት በቡላፔ ከተማ መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
#gazette_plus
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢቦላ ወረርሽኝ 31 ሰዎች መሞታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ በዚህ ወር ውስጥ ብቻ 48 ሰዎች በኢቦላ ተይዘዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት አስፈላጊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን በማድረስ፣ ባለሙያዎችን በማሰማራትና የኢቦላ ህክምና ማዕከል በማቋቋም ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ገልጸዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀው በሽታው ቀደም ሲል በሁለት ወረዳዎች ተከስቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ወደ አራት ወረዳዎች ተዛምቷል።
ወረርሽኙ ከሶስት ዓመታት በኋላ የታወጀው ከሁለት ሳምንት በፊት በቡላፔ ከተማ መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
#gazette_plus
9 months ago