Logo
YenetaTube
በኮንጎ 31 ሰዎች በኢቦላ ሞቱ

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢቦላ ወረርሽኝ 31 ሰዎች መሞታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም እንደተናገሩት፤ በሀገሪቷ በዚህ ወር ውስጥ ብቻ 48 ሰዎች በኢቦላ ተይዘዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት አስፈላጊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን በማድረስ፣ ባለሙያዎችን በማሰማራትና የኢቦላ ህክምና ማዕከል በማቋቋም ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ገልጸዋል።

የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀው በሽታው ቀደም ሲል በሁለት ወረዳዎች ተከስቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ወደ አራት ወረዳዎች ተዛምቷል።

ወረርሽኙ ከሶስት ዓመታት በኋላ የታወጀው ከሁለት ሳምንት በፊት በቡላፔ ከተማ መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
#gazette_plus

9 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.