4 months ago
በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ያለመው "ኤድቴክ ሳምንት 2026" መካሄድ ጀምሯል
#ethiopia | በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ያለመው ሁለተኛው የ"ኢትዮጵያ ኤድቴክ ሳምንት" በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
ሪች ፎር ቼንጅ ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዘርፉ ተመራማሪዎችና ስራ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል።
"ቴክኖሎጂን ለሁሉ አሳታፊና ጾታን መሰረት ላደረገ ትምህርት ማዋል" በሚል መሪ ቃል በሳይንስ ሙዚየም መካሄድ የጀመረው ይህ መድረክ፤ በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪዎች የደረሱበትን ደረጃ ለማሳየትና ከባለሀብቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ባይሳ በዳዳ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የጀመረችውን ዲጂታል ሽግግር ለማሳካት የትምህርት ስርአቱን በቴክኖሎጂ መደገፍ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
ባለፉት ጥቂት አመታት በሀገሪቱ የነበሩ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ቁጥር ከ50 ወደ 300 ማደጉን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ይህም ከ30 ሺህ በላይ የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል።
"ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ ትልቅ ውጤት እያመጣ ነው።
ቴክኖሎጂ ግብ ሳይሆን የዜጎችን ህይወት ማሻሻያ መሳሪያ ነው።
ስራ ፈጣሪዎች የሚያመጧቸው አዳዲስ ሀሳቦች በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆኑ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል"ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአማካሪዎች ሰብሳቢና የክልል ተጠሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ መንግስት የብሄራዊ ፈተናዎችን በዲጂታል መንገድ ለመስጠት የጀመረው ጥረት የዘርፉን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።
ቴክኖሎጂው ተደራሽነቱ ከከተማ አልፎ ገጠር ለሚገኙ ተማሪዎችና ሴቶች እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራም አክለዋል።
የሪች ፎር ቼንጅ ግሎባል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሶፊያ ብሬትሆልትስ በበኩላቸው፤ ድርጅታቸው ባለፉት ሶስት አመታት 34 የኤድቴክ ስራ ፈጣሪዎችን በመደገፍ ከ400 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ትኩረቱ አዳዲስ ፈጠራዎችን ከመሞከር ባለፈ በስፋት ወደ ትምህርት ስርአቱ እንዲገቡ (Scale-up) ማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።
በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የፈጠራ ትምህርት ማእከል ዳይሬክተር ዋዲኮ ዋይታ፤ ቴክኖሎጂ መምህራንን የሚተካ ሳይሆን የሚያግዝ መሆን እንዳለበትና ወጣቶች ለነገው የስራ አለም ብቁ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
ለሚቀጥሉት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ስራ ፈጣሪዎች የፈጠራ ውጤቶቻቸውን ለእይታ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ከፖሊሲ አውጪዎችና ከአጋር አካላት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ታውቋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopia #edtechweek2026 #educationtechnology #digitalethiopia #reachforchange #mastercardfoundation #innovation #getutemesgen #moe #mint
#ethiopia | በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል ያለመው ሁለተኛው የ"ኢትዮጵያ ኤድቴክ ሳምንት" በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
ሪች ፎር ቼንጅ ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዘርፉ ተመራማሪዎችና ስራ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል።
"ቴክኖሎጂን ለሁሉ አሳታፊና ጾታን መሰረት ላደረገ ትምህርት ማዋል" በሚል መሪ ቃል በሳይንስ ሙዚየም መካሄድ የጀመረው ይህ መድረክ፤ በኢትዮጵያ የትምህርት ቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪዎች የደረሱበትን ደረጃ ለማሳየትና ከባለሀብቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ባይሳ በዳዳ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የጀመረችውን ዲጂታል ሽግግር ለማሳካት የትምህርት ስርአቱን በቴክኖሎጂ መደገፍ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
ባለፉት ጥቂት አመታት በሀገሪቱ የነበሩ የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ቁጥር ከ50 ወደ 300 ማደጉን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ይህም ከ30 ሺህ በላይ የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረዋል።
"ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ ትልቅ ውጤት እያመጣ ነው።
ቴክኖሎጂ ግብ ሳይሆን የዜጎችን ህይወት ማሻሻያ መሳሪያ ነው።
ስራ ፈጣሪዎች የሚያመጧቸው አዳዲስ ሀሳቦች በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆኑ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል"ብለዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአማካሪዎች ሰብሳቢና የክልል ተጠሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ መንግስት የብሄራዊ ፈተናዎችን በዲጂታል መንገድ ለመስጠት የጀመረው ጥረት የዘርፉን ትኩረት ያሳያል ብለዋል።
ቴክኖሎጂው ተደራሽነቱ ከከተማ አልፎ ገጠር ለሚገኙ ተማሪዎችና ሴቶች እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራም አክለዋል።
የሪች ፎር ቼንጅ ግሎባል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሶፊያ ብሬትሆልትስ በበኩላቸው፤ ድርጅታቸው ባለፉት ሶስት አመታት 34 የኤድቴክ ስራ ፈጣሪዎችን በመደገፍ ከ400 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ትኩረቱ አዳዲስ ፈጠራዎችን ከመሞከር ባለፈ በስፋት ወደ ትምህርት ስርአቱ እንዲገቡ (Scale-up) ማድረግ መሆኑን አመልክተዋል።
በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የፈጠራ ትምህርት ማእከል ዳይሬክተር ዋዲኮ ዋይታ፤ ቴክኖሎጂ መምህራንን የሚተካ ሳይሆን የሚያግዝ መሆን እንዳለበትና ወጣቶች ለነገው የስራ አለም ብቁ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
ለሚቀጥሉት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ስራ ፈጣሪዎች የፈጠራ ውጤቶቻቸውን ለእይታ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ከፖሊሲ አውጪዎችና ከአጋር አካላት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ታውቋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopia #edtechweek2026 #educationtechnology #digitalethiopia #reachforchange #mastercardfoundation #innovation #getutemesgen #moe #mint
Comments