5 months ago
350 ሺህ ዶላር :
ኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በዋሽንግተን ዲሲ አሰባሰበ
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ ትላንት መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ማርዮት ሆቴል ባከናወነው የማጠቃለያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 350 ሺህ ዶላር በማግኘት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን የድርጅቱ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ብርሃን ተድላ አስታውቀዋል።
እስካሁን 110 ሺህ ዶላር በቀጥታ በባንክ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ቀሪው ቃል የተገባና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚሰበሰብ ነው።
በተገኘው ገንዘብ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ በወረፋ ላይ ለሚገኙ 120 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ለመስጠት ዕቅድ ተይዟል።
ከጣሊያን ከመጡ ሦስት ድርጅቶች ጋር በመተባበር 50 ተጨማሪ ሕፃናትን ለማከም ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው። ይህም በቅርብ ወራት ውስጥ ሕክምና የሚያገኙ ሕፃናትን ቁጥር 170 ያደርሰዋል።
በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ በአራት የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ጥገና ማዕከላትን ለማቋቋም ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ወጣት አዶናይ ብርሃነ፣ ወይዘሮ ሐና ክብሩና ባለቤታቸው ሳሚ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዝግጅቱ ላይ የዋሽንግተን ዲሲ እጩ ከንቲባ ሚስተር ኬኒየን ማክደፊ፣ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል እና ሊቀ ማዕምራን ፕሮፌሰር ዘበነ ለማን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ ኢትዮጵያውያን የልብ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አዲስ የሚቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን እንዲቀላቀሉና ወገኖቻቸውን እንዲረዱ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #ethiopiannews #hearttoheart #childrenshealth #fundraising #washingtondc #ethiopiandiaspora #heartsurgery #charity #የልብሕሙማን #ሰብአዊነት #ዋሽንግተንዲሲ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በዋሽንግተን ዲሲ አሰባሰበ
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ ትላንት መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ማርዮት ሆቴል ባከናወነው የማጠቃለያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 350 ሺህ ዶላር በማግኘት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን የድርጅቱ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ብርሃን ተድላ አስታውቀዋል።
እስካሁን 110 ሺህ ዶላር በቀጥታ በባንክ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ቀሪው ቃል የተገባና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚሰበሰብ ነው።
በተገኘው ገንዘብ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ በወረፋ ላይ ለሚገኙ 120 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ለመስጠት ዕቅድ ተይዟል።
ከጣሊያን ከመጡ ሦስት ድርጅቶች ጋር በመተባበር 50 ተጨማሪ ሕፃናትን ለማከም ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው። ይህም በቅርብ ወራት ውስጥ ሕክምና የሚያገኙ ሕፃናትን ቁጥር 170 ያደርሰዋል።
በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ በአራት የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ጥገና ማዕከላትን ለማቋቋም ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ወጣት አዶናይ ብርሃነ፣ ወይዘሮ ሐና ክብሩና ባለቤታቸው ሳሚ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዝግጅቱ ላይ የዋሽንግተን ዲሲ እጩ ከንቲባ ሚስተር ኬኒየን ማክደፊ፣ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል እና ሊቀ ማዕምራን ፕሮፌሰር ዘበነ ለማን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ ኢትዮጵያውያን የልብ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አዲስ የሚቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን እንዲቀላቀሉና ወገኖቻቸውን እንዲረዱ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #ethiopiannews #hearttoheart #childrenshealth #fundraising #washingtondc #ethiopiandiaspora #heartsurgery #charity #የልብሕሙማን #ሰብአዊነት #ዋሽንግተንዲሲ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
🕯️ የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሽኝት መርሐ-ግብር
በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሚከናወነው የታዋቂው መምህር ዘለዓለም ወንድሙ የአስክሬን ሽኝት መርሐ-ግብር ዝርዝር ይፋ ሆኗል። መርሐ-ግብሩ ከዛሬ እሑድ ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ድረስ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ይከናወናል።
የጊዜ ሰሌዳ (ዋሽንግተን ዲሲ)
፩. እሑድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይከናወናል።
የሀዘን መግለጫ፦
ከቅዳሴ በኋላ በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የላይኛው መኪና ማቆሚያ ላይ አገልጋዮችና ምእመናን ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
፪. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026)
ለቅሶ መድረሻ፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) - 10:00 (4pm) ሰዓት በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ክፍት ይሆናል።
የሠርክ ጸሎት፦ ከቀኑ 10:30 (4:30pm) - 1:30 (7:30pm) በትምህርተ ወንጌልና በውዳሴ ማርያም መዝከር ይከናወናል።
ወደ ቤተክርስቲያን መግባት፦ ከምሽቱ 1:00 (7pm) ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተክርስቲያን ይገባል።
የሌሊት ማህሌት፦ ከሌሊቱ 7:00 (1am) ጀምሮ አገልጋዮችና ምእመናን ሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
፫. ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም (March 10, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ ከጠዋቱ 3:00 (9am) - 6:00 (12pm) ይከናወናል።
ምስክርነት፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) ጀምሮ የሕይወት ታሪክና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ፦ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ይሰጣል።
ሽኝት፦ ከሥነ-ሥርዓቱ በኋላ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ይደረግለታል።
⚠️ ጠቃሚ ማሳሰቢያዎች
የአለባበስ ሥርዓት፦
በፍትሐቱና በሽኝቱ ላይ የሚገኙ አገልጋዮችና ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሰው እንዲገኙ በአክብሮት ተጠይቀዋል።
አድራሻ፦
1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
"ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሰ ገብረከ ወልደ ሰማዕት!"
(አቤቱ የባሪያህን የወልደ ሰማዕትን ነፍስ አሳርፍ!)
የመምህራችንን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን፤ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥልን።
#መምህርዘለዓለምወንድሙ #ወልደሰማዕት #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ዋሽንግተንዲሲ #ሽኝት #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሚከናወነው የታዋቂው መምህር ዘለዓለም ወንድሙ የአስክሬን ሽኝት መርሐ-ግብር ዝርዝር ይፋ ሆኗል። መርሐ-ግብሩ ከዛሬ እሑድ ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ድረስ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ይከናወናል።
የጊዜ ሰሌዳ (ዋሽንግተን ዲሲ)
፩. እሑድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይከናወናል።
የሀዘን መግለጫ፦
ከቅዳሴ በኋላ በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የላይኛው መኪና ማቆሚያ ላይ አገልጋዮችና ምእመናን ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
፪. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026)
ለቅሶ መድረሻ፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) - 10:00 (4pm) ሰዓት በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ክፍት ይሆናል።
የሠርክ ጸሎት፦ ከቀኑ 10:30 (4:30pm) - 1:30 (7:30pm) በትምህርተ ወንጌልና በውዳሴ ማርያም መዝከር ይከናወናል።
ወደ ቤተክርስቲያን መግባት፦ ከምሽቱ 1:00 (7pm) ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተክርስቲያን ይገባል።
የሌሊት ማህሌት፦ ከሌሊቱ 7:00 (1am) ጀምሮ አገልጋዮችና ምእመናን ሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
፫. ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም (March 10, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ ከጠዋቱ 3:00 (9am) - 6:00 (12pm) ይከናወናል።
ምስክርነት፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) ጀምሮ የሕይወት ታሪክና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ፦ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ይሰጣል።
ሽኝት፦ ከሥነ-ሥርዓቱ በኋላ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ይደረግለታል።
⚠️ ጠቃሚ ማሳሰቢያዎች
የአለባበስ ሥርዓት፦
በፍትሐቱና በሽኝቱ ላይ የሚገኙ አገልጋዮችና ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሰው እንዲገኙ በአክብሮት ተጠይቀዋል።
አድራሻ፦
1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
"ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሰ ገብረከ ወልደ ሰማዕት!"
(አቤቱ የባሪያህን የወልደ ሰማዕትን ነፍስ አሳርፍ!)
የመምህራችንን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን፤ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥልን።
#መምህርዘለዓለምወንድሙ #ወልደሰማዕት #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ዋሽንግተንዲሲ #ሽኝት #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
Comments