5 months ago
" ኢትዮጵያ ትቅደም '’
መፈክር የፈጠሩት አቶ ከበደ አኒሳ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት መሐከል አንዱ ነበሩ። አቶ ከበደ አኒሳ ጎሮ ታህሳስ 19 ቀን 1924 በቀድሞው አጠራር ወለጋ ጠቅላይ ግዛት ነቀምት ከተማ ተወልደው እዚያው ነቀምት የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ትምህርት ቤት ካጠናቀቁ በኋላ በተከታታይ በአዲስ አበባ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።ወደ ውጭ በማቅናትም በቆጵሮስና እስራኤል ማህበራዊ ሳይንስ በአሜሪካን ማካለስተር ኮሌጅ ጋዜጠኝነት ተምረዋል።
#ከዚያም በተማሩት ሙያዎች በመምህርነት፣ በትምህርት ቤት ሥራ መሪነት፣በኢንስፔክተርነት ለአሥር ዓመታት ከዚያም በማስታወቂያ ሚኒስቴር፣ በአገር አስተዳደር ሚኒስቴር፣ ሕዝባዊ ኑሮ እድገትና ዘመቻ መምሪያ ለሃያ ሰባት ዓመታት በጠቅላላው ለ37 ዓመታት አገራቸውን አገልግለዋል።
#አቶ ከበደ አኒሳ በልዩ ልዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ የሠሩ ከመሆናቸው ጋር በጋዜጠኝነት ሙያቸው የታወቁ ነበሩ። በራሳቸው አንደበት ከተናገሩትና በጽሑፍም ካስቀመጡት ማስታወሻ በኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅነት፣በአሜሪካን ድምፅ ሪፖርተርነት፣እንዲሁም ለኢትዮጵያን ሔራልድ የሠራሁበትን ጊዜ በጣም እኮራበታለሁ ብለዋል።
"በጋዜጠኝነቴ ዘመን የላቀ ደስታ የሰጠኝ ነገር ቢኖር ይላሉ አቶ ከበደ"የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣ ላይ መሪ መፈክር አድርጌ ያስቀመጥኩት "ኢትዮጵያ ትቅደም” የሚለው ቃል ነው። ይህንን የፃፍኩት ደርግ ከመፈጠሩ ዘጠኝ ዓመታት በፊት በ1957 ነው'’ በማለት ጽፈዋል። የሙያ አጋራቸው የሆኑትና ከ35 ዓመታት በላይ የቅርብ ወዳጃቸው የሆኑት አንጋፋው የሮይተርስ ጋዜጠኛ አቶ ፀጋዬ ታደሰ በሰጡት ምስክርነት " በወቅቱ ቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ኢትዮጵያ ትቅደም ስትል ምን ማለትህ ነበር ብለው ጠይቀውት ነበር። እሱም"ኢትዮጵያን ስለምወድ፣ሕዝቡንም ስለማከብር ሃገሬ በሁሉ ነገር ቀድማ ማየት ስለምፈልግ ነው ብሎ መልሷል። የረዢም ጊዜ ጓደኛዬ ነበረ። ሲለየኝ በጣም አዝኛለሁ።" ብለዋል።
#እኚህ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለብዙ ዓመታት በጋዜጠኝነት ሲያገለግሉ ብዙዎቻችን የሙያችን ተምሳሌትና ለኛም እንደ አባት የምናያቸው ድንቅ ጋዜጠኛ ነበሩ::አቶ ከበደ አኒሳ የዘጠኝ ልጆች አባት ሲሆኑ ስምንት የልጅ ልጆችን አይተዋል።
✍️Guenet Ayele Gruenberg
#ኢትዮጵያትቅደም
#enkssm #ethiopianhistoryandtourism
መፈክር የፈጠሩት አቶ ከበደ አኒሳ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት መሐከል አንዱ ነበሩ። አቶ ከበደ አኒሳ ጎሮ ታህሳስ 19 ቀን 1924 በቀድሞው አጠራር ወለጋ ጠቅላይ ግዛት ነቀምት ከተማ ተወልደው እዚያው ነቀምት የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ትምህርት ቤት ካጠናቀቁ በኋላ በተከታታይ በአዲስ አበባ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።ወደ ውጭ በማቅናትም በቆጵሮስና እስራኤል ማህበራዊ ሳይንስ በአሜሪካን ማካለስተር ኮሌጅ ጋዜጠኝነት ተምረዋል።
#ከዚያም በተማሩት ሙያዎች በመምህርነት፣ በትምህርት ቤት ሥራ መሪነት፣በኢንስፔክተርነት ለአሥር ዓመታት ከዚያም በማስታወቂያ ሚኒስቴር፣ በአገር አስተዳደር ሚኒስቴር፣ ሕዝባዊ ኑሮ እድገትና ዘመቻ መምሪያ ለሃያ ሰባት ዓመታት በጠቅላላው ለ37 ዓመታት አገራቸውን አገልግለዋል።
#አቶ ከበደ አኒሳ በልዩ ልዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ የሠሩ ከመሆናቸው ጋር በጋዜጠኝነት ሙያቸው የታወቁ ነበሩ። በራሳቸው አንደበት ከተናገሩትና በጽሑፍም ካስቀመጡት ማስታወሻ በኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅነት፣በአሜሪካን ድምፅ ሪፖርተርነት፣እንዲሁም ለኢትዮጵያን ሔራልድ የሠራሁበትን ጊዜ በጣም እኮራበታለሁ ብለዋል።
"በጋዜጠኝነቴ ዘመን የላቀ ደስታ የሰጠኝ ነገር ቢኖር ይላሉ አቶ ከበደ"የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣ ላይ መሪ መፈክር አድርጌ ያስቀመጥኩት "ኢትዮጵያ ትቅደም” የሚለው ቃል ነው። ይህንን የፃፍኩት ደርግ ከመፈጠሩ ዘጠኝ ዓመታት በፊት በ1957 ነው'’ በማለት ጽፈዋል። የሙያ አጋራቸው የሆኑትና ከ35 ዓመታት በላይ የቅርብ ወዳጃቸው የሆኑት አንጋፋው የሮይተርስ ጋዜጠኛ አቶ ፀጋዬ ታደሰ በሰጡት ምስክርነት " በወቅቱ ቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ኢትዮጵያ ትቅደም ስትል ምን ማለትህ ነበር ብለው ጠይቀውት ነበር። እሱም"ኢትዮጵያን ስለምወድ፣ሕዝቡንም ስለማከብር ሃገሬ በሁሉ ነገር ቀድማ ማየት ስለምፈልግ ነው ብሎ መልሷል። የረዢም ጊዜ ጓደኛዬ ነበረ። ሲለየኝ በጣም አዝኛለሁ።" ብለዋል።
#እኚህ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለብዙ ዓመታት በጋዜጠኝነት ሲያገለግሉ ብዙዎቻችን የሙያችን ተምሳሌትና ለኛም እንደ አባት የምናያቸው ድንቅ ጋዜጠኛ ነበሩ::አቶ ከበደ አኒሳ የዘጠኝ ልጆች አባት ሲሆኑ ስምንት የልጅ ልጆችን አይተዋል።
✍️Guenet Ayele Gruenberg
#ኢትዮጵያትቅደም
#enkssm #ethiopianhistoryandtourism
Comments