3 months ago
አዲስ አበባን የረገትጥኩ ሰሞን
(ዘላለም ጸጋዬ)
#ethiopia | ምንም እንኩዋን የተወለድኩት ከአንዲት ትንሽዬ የገጠር ከተማ ቢሆንም የልጅነት አይኔን ስገልጥ ግን የማስታውሰው የማርያምን ቤተክርስትያን፣ የመቅድስዋን የእጣን ሽታ፣የንፋስ ሽውታ የሚያስፉዋጨውን የጉዋሮዋን አርዘሊባኖስ፣የደጀ ሰላምዋን መአዛ ፣ካጠገቡም ያለውን ጭው ያለ ገደል እንዲሁም "መልእክተ ዮሀንስ ሀዋርያ ወልደ ዘብድዮስ" እያሉ መርጌታ አየለን የከበቡ የቆሎ ተማሪዎች ድምጽ እና የመሳሰለው ነው።በጥቅሉ የልጅነት አይኔን የገለጥኩት ስልጣኔ ካልጎበኘው እልም ካለ ገጠር ውስጥ ነው ...እናማ አኩፋዳዬን ጣጥዬ አዲስ አበባ የገባሁት የሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነበር።ነፍሱን ይማረውና አባቴ ፈለገ ዮርዲያኖስ ትምህርት ቤት ወስዶ ከተተኝ።አባቴ ቀድሞ ከተማ ገብቶ አስኩዋላት ተምሮ እቀድሞዋ ቺኮዝሎቫኪያ ድረስም ሂዶ ተምሮ ነበር የመጣው።ተያም በሁዋላ እስከ ደርግ ምክርቤት አባልነት ደርሶ ነበር።
ትምህርት የተጀመረ ሰሞን የእርሻ መመህራችን ስለ ስንዴ አበቃቀል ሲያስተምሩ ቆይተው።"ጥያቄያለው አለ?" ሲሉ ከመቅጽበት እጄን እንደ ኢራን ሚሳኤል ዘረጋሁት።እኔ በገጠር አያለሁ የማውቀው ትልቅ ስራ መምህረነት ነው።ከዛ ባለፈ ሁሉም አርሶ ነው የሚበላ።እናም ከተማ ከገባሁበት ቀን ጀምሮ ስትከነክነኝ የከረመችውን ጥያቄ እንዲህ በማለት አቀረብኩ "መምህር የስንዴ አበቃቀልን አላጣሁትም የኔ ጥያቄ ግን... እንዲያው ለመሆኑ ይሄ ሁሉ ከተሜ የት አርሶ ነው የሚበላ" ብዬ ስጠይቅ...የክፍሉ ተማሪ ሁሉ በሳቅ ፈረሰ።ያልሳቀ አንድ ሰው ቢኖር መምህሩ ብቻ ነበሩ።እንዴ ምንድነው አዳሜን ሚያስቀው ብዬ ተገረምኩ።አባቴ በሰው ላይ መሳቅ እና ማላገጥ አይገባም እንዲይ ካደረግክ ነገ ሌሎች በአንተ ላይ ያላግጡብሀል ይለኝ ነበር።በገጠርም ቢሆን ምን አልባት ነጠላችንን አፋችን ላይ ጣል አርገን በትንሹ ብናንጉዋጥጥ ነውይ በሰው ላይ ካካካክ ብለን አንስቅም።
የእርሻ ክፍለ ግዜው እንዳለቀ።መምህሩ ሲወጡ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ እየተከተለ "ዘላለም ገበሬው" ማለት ጀመረ።ምንም አልተደናገጥኩም።ድሮም ደንቆሮ ወሬ አያጣም ብዬ ኮስተር አልኩ።የገጠር ልጅ ልበሙሉ አይደል።እህኔ እኮ የአንዱን ተማሪ የአይን መጋረጃ በዚህ አፈር ሲግፍ በከረመ እጄ ብከድንለት እኮ ሌላው አርፎ ይቀመጥ ነበር ብዬ አሰብኩ። ነገር ግን ከክላስ ስወጣ ወይም ስኔ 30 ጠብቀው ጨርቆስ ጉሊት መሃል ተሰብስበው ዱቄት እንዳያደርጉኝ ደግሞ ፈራሁ።በዛ ላይ ሰፈሩ ብዙ ግዜ በችግር ብዛት በህይወት አረቄ ሰክረው የሚደባደቡ አያጣውም ነበር።
የሆነው ሆኖ እንዲህ አልኩዋቸው...አዎ ገበሬ ነኝ።የገበሬ ምርቱ በትሳስ ነው።ታህሳስ ላይ እንገናኝ አልኩዋቸው።ቅኔ መሆኑዋ ነበር።የተሳዳቢው ተማሪ ቡድን መሪ ደግሞ አንዲት ድፍኑዋን ጨረቃ የመሰለች ዘቢብ የምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረች።ቆንጆ ሰው አመሉም እንደመልኩ ሸጋ፣ልቡም እንደ እጣን ንጹህ ይመስለኝ ነበር።ገና ያኔ ነው አዬ ውበት ከንቱ ደምግባትም ብላሽ ያልኩት::ዘቢብ ግን ዛሬ የት ነሽ...እነዛ እንደ ቤተመቅደስ ጧፍ የሚያበሩ አይኖችሽ ሰላም ናቸው ወይ??? አቤት ውበታቸው አይን ያስፈነጥዝ ነበር•••
የሆነው ሆኖ በመጨረሻም ታህሳስ የመጀመርያ ሴሚስተር ውጤት ሲመጣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣሁ።ያሁሉ ተማሪ እንደ ንጉስ ያየኝ ጀመር።እኔም ቆፍጠን ቄምጨጭ አልኩ "አለም ምንግዜም የቆራጦች ናት" ይል ነበር በዓሉ ግርማ።እናማ በክፍላችን ውስጥ እንግሊዘኛን እንደኔ የሚያነባት አልነበረም።አፌን ያዝ ከሚያደርገኝ የገጠር አማርኛ በስተቀር ምንም የሚወጣልኝ አልነበረም።ከባድ ጥያቄ በተጠየቀ ቁጠር መምህራን አይናቸውን ወደኔ ነበር የሚያቆለቁሉት።
ውሸት የሚባል አላውቅም ነበር።አሁንም ይተናነቀኛል።"እናትክን" የሚል ስድብ የሰማሁት እዛው ከትምህርት ቤታችን ፊትለፊት ከጉሊቱ መካከል ነበር።የዛን ቀን ከሰማይ እሳት እና ምስማር ቀላቅሎ የሚጥል ነበር የመሰለኝ።ያለወላጅ እናት ስላደግኩ በሱዋ ምትክ በልቤ እመቤታችን ንጽህት ድንግል ማርያም እናቴ እያልኩ ስላደግኩ እሱዋ የተሰደበች ያክል ነበር የሰቀጠጠኝ።በዛ ላይ ደግሞ "በእንተ ስሙዋ ለማርያም" ያልኩበት በስሙዋ ተማጽኜ ጎርሼ ያደርኩበት ዘመን ውልብ አለብኝ።
ምንም እንኩዋን አዲስ አበባ አቀባበሉዋ እንደ ደንባራ በቅሎ መንቃራ ቢሆንም።ኢለመንታሪ ፈለገ ዮርዳኖስ፣ ሀይስኩል 9 እና 10 አብዮት ቅርስ፣ 11 እና 12 ቦሌ ሀይስኩል፣ እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድረስ አንቀባርራ አሳድጋኛለች።ከገጠር ይዤ የወጣሁት ስብእና ለዛሬው ማንነቴ እጅጉን አስተዋጽኦ አድርጉዋል።አንዳንዱም ጎጂ ባህል ነበር ለምሳሌ ሳልደርስበት የደረሰብኝን ሰው ሳልበቀል መተው ሽንፈት ይመስለኛል።እርቅም ከታሰበ ከተመጣጣኝ አጻፋ በቀል በሁዋላ እንጂ እንዲሁ አንተም ተው አንተም ተው አይሰራም።
ለማንኛውም አዲስ አበባ ቤቴ፣አሳዳጊዬ ክፉውንም፣ ደጉንም ያሳለፍኩብሽ፣ የኔ ሁሉን ቻይ ኑሪልኝ።ምንም እንኳን ባህር ብሻገርም ልቤ ግን ያለው ካንቺው ዘንድ ነው።•••የሰው ልጅ ከመኖር የሚያተርፈው ትዝታ ነው።
እኔም እነሆ ትዝታዬን አጋራኋችሁ!
መልካም ሰንበት!
(ዘላለም ጸጋዬ)
#ethiopia | ምንም እንኩዋን የተወለድኩት ከአንዲት ትንሽዬ የገጠር ከተማ ቢሆንም የልጅነት አይኔን ስገልጥ ግን የማስታውሰው የማርያምን ቤተክርስትያን፣ የመቅድስዋን የእጣን ሽታ፣የንፋስ ሽውታ የሚያስፉዋጨውን የጉዋሮዋን አርዘሊባኖስ፣የደጀ ሰላምዋን መአዛ ፣ካጠገቡም ያለውን ጭው ያለ ገደል እንዲሁም "መልእክተ ዮሀንስ ሀዋርያ ወልደ ዘብድዮስ" እያሉ መርጌታ አየለን የከበቡ የቆሎ ተማሪዎች ድምጽ እና የመሳሰለው ነው።በጥቅሉ የልጅነት አይኔን የገለጥኩት ስልጣኔ ካልጎበኘው እልም ካለ ገጠር ውስጥ ነው ...እናማ አኩፋዳዬን ጣጥዬ አዲስ አበባ የገባሁት የሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነበር።ነፍሱን ይማረውና አባቴ ፈለገ ዮርዲያኖስ ትምህርት ቤት ወስዶ ከተተኝ።አባቴ ቀድሞ ከተማ ገብቶ አስኩዋላት ተምሮ እቀድሞዋ ቺኮዝሎቫኪያ ድረስም ሂዶ ተምሮ ነበር የመጣው።ተያም በሁዋላ እስከ ደርግ ምክርቤት አባልነት ደርሶ ነበር።
ትምህርት የተጀመረ ሰሞን የእርሻ መመህራችን ስለ ስንዴ አበቃቀል ሲያስተምሩ ቆይተው።"ጥያቄያለው አለ?" ሲሉ ከመቅጽበት እጄን እንደ ኢራን ሚሳኤል ዘረጋሁት።እኔ በገጠር አያለሁ የማውቀው ትልቅ ስራ መምህረነት ነው።ከዛ ባለፈ ሁሉም አርሶ ነው የሚበላ።እናም ከተማ ከገባሁበት ቀን ጀምሮ ስትከነክነኝ የከረመችውን ጥያቄ እንዲህ በማለት አቀረብኩ "መምህር የስንዴ አበቃቀልን አላጣሁትም የኔ ጥያቄ ግን... እንዲያው ለመሆኑ ይሄ ሁሉ ከተሜ የት አርሶ ነው የሚበላ" ብዬ ስጠይቅ...የክፍሉ ተማሪ ሁሉ በሳቅ ፈረሰ።ያልሳቀ አንድ ሰው ቢኖር መምህሩ ብቻ ነበሩ።እንዴ ምንድነው አዳሜን ሚያስቀው ብዬ ተገረምኩ።አባቴ በሰው ላይ መሳቅ እና ማላገጥ አይገባም እንዲይ ካደረግክ ነገ ሌሎች በአንተ ላይ ያላግጡብሀል ይለኝ ነበር።በገጠርም ቢሆን ምን አልባት ነጠላችንን አፋችን ላይ ጣል አርገን በትንሹ ብናንጉዋጥጥ ነውይ በሰው ላይ ካካካክ ብለን አንስቅም።
የእርሻ ክፍለ ግዜው እንዳለቀ።መምህሩ ሲወጡ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ እየተከተለ "ዘላለም ገበሬው" ማለት ጀመረ።ምንም አልተደናገጥኩም።ድሮም ደንቆሮ ወሬ አያጣም ብዬ ኮስተር አልኩ።የገጠር ልጅ ልበሙሉ አይደል።እህኔ እኮ የአንዱን ተማሪ የአይን መጋረጃ በዚህ አፈር ሲግፍ በከረመ እጄ ብከድንለት እኮ ሌላው አርፎ ይቀመጥ ነበር ብዬ አሰብኩ። ነገር ግን ከክላስ ስወጣ ወይም ስኔ 30 ጠብቀው ጨርቆስ ጉሊት መሃል ተሰብስበው ዱቄት እንዳያደርጉኝ ደግሞ ፈራሁ።በዛ ላይ ሰፈሩ ብዙ ግዜ በችግር ብዛት በህይወት አረቄ ሰክረው የሚደባደቡ አያጣውም ነበር።
የሆነው ሆኖ እንዲህ አልኩዋቸው...አዎ ገበሬ ነኝ።የገበሬ ምርቱ በትሳስ ነው።ታህሳስ ላይ እንገናኝ አልኩዋቸው።ቅኔ መሆኑዋ ነበር።የተሳዳቢው ተማሪ ቡድን መሪ ደግሞ አንዲት ድፍኑዋን ጨረቃ የመሰለች ዘቢብ የምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረች።ቆንጆ ሰው አመሉም እንደመልኩ ሸጋ፣ልቡም እንደ እጣን ንጹህ ይመስለኝ ነበር።ገና ያኔ ነው አዬ ውበት ከንቱ ደምግባትም ብላሽ ያልኩት::ዘቢብ ግን ዛሬ የት ነሽ...እነዛ እንደ ቤተመቅደስ ጧፍ የሚያበሩ አይኖችሽ ሰላም ናቸው ወይ??? አቤት ውበታቸው አይን ያስፈነጥዝ ነበር•••
የሆነው ሆኖ በመጨረሻም ታህሳስ የመጀመርያ ሴሚስተር ውጤት ሲመጣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣሁ።ያሁሉ ተማሪ እንደ ንጉስ ያየኝ ጀመር።እኔም ቆፍጠን ቄምጨጭ አልኩ "አለም ምንግዜም የቆራጦች ናት" ይል ነበር በዓሉ ግርማ።እናማ በክፍላችን ውስጥ እንግሊዘኛን እንደኔ የሚያነባት አልነበረም።አፌን ያዝ ከሚያደርገኝ የገጠር አማርኛ በስተቀር ምንም የሚወጣልኝ አልነበረም።ከባድ ጥያቄ በተጠየቀ ቁጠር መምህራን አይናቸውን ወደኔ ነበር የሚያቆለቁሉት።
ውሸት የሚባል አላውቅም ነበር።አሁንም ይተናነቀኛል።"እናትክን" የሚል ስድብ የሰማሁት እዛው ከትምህርት ቤታችን ፊትለፊት ከጉሊቱ መካከል ነበር።የዛን ቀን ከሰማይ እሳት እና ምስማር ቀላቅሎ የሚጥል ነበር የመሰለኝ።ያለወላጅ እናት ስላደግኩ በሱዋ ምትክ በልቤ እመቤታችን ንጽህት ድንግል ማርያም እናቴ እያልኩ ስላደግኩ እሱዋ የተሰደበች ያክል ነበር የሰቀጠጠኝ።በዛ ላይ ደግሞ "በእንተ ስሙዋ ለማርያም" ያልኩበት በስሙዋ ተማጽኜ ጎርሼ ያደርኩበት ዘመን ውልብ አለብኝ።
ምንም እንኩዋን አዲስ አበባ አቀባበሉዋ እንደ ደንባራ በቅሎ መንቃራ ቢሆንም።ኢለመንታሪ ፈለገ ዮርዳኖስ፣ ሀይስኩል 9 እና 10 አብዮት ቅርስ፣ 11 እና 12 ቦሌ ሀይስኩል፣ እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድረስ አንቀባርራ አሳድጋኛለች።ከገጠር ይዤ የወጣሁት ስብእና ለዛሬው ማንነቴ እጅጉን አስተዋጽኦ አድርጉዋል።አንዳንዱም ጎጂ ባህል ነበር ለምሳሌ ሳልደርስበት የደረሰብኝን ሰው ሳልበቀል መተው ሽንፈት ይመስለኛል።እርቅም ከታሰበ ከተመጣጣኝ አጻፋ በቀል በሁዋላ እንጂ እንዲሁ አንተም ተው አንተም ተው አይሰራም።
ለማንኛውም አዲስ አበባ ቤቴ፣አሳዳጊዬ ክፉውንም፣ ደጉንም ያሳለፍኩብሽ፣ የኔ ሁሉን ቻይ ኑሪልኝ።ምንም እንኳን ባህር ብሻገርም ልቤ ግን ያለው ካንቺው ዘንድ ነው።•••የሰው ልጅ ከመኖር የሚያተርፈው ትዝታ ነው።
እኔም እነሆ ትዝታዬን አጋራኋችሁ!
መልካም ሰንበት!
3 months ago
የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ
ወንድም ተዋበ ወንድሙ እንዳነበበው
#ethiopia | የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ቤተሰቦችና የመምህር ዘላለም ወዳጆች፤ ዛሬ የምንናገረው ስለ አንድ ሥጋዊ ወንድማችን ብቻ አይደለም፤ የምንናገረው ስለ ብዙዎች አባት፣ ስለ ድሆች ረዳትና ስለ ወንጌል ብርሃን ነው። መምህር ዘላለምን በሥጋ መለየታችን ለአንጀታችን እጅግ የሚከብድ፣ ለቤተሰባችንም መሪር ሐዘን ቢሆንብንም፤ እርሱ ግን አስቀድሞ በመልካም ሥራው በሰማይ ቤት ቤቱን ሰርቶ እንደነበር እናምናለን።
ምንም እንኳን በሰውነታችን ብናዝንም፣ በብጹዓን አባቶቻችን ጸሎትና ትምህርት፣ እንዲሁም በዚህ በመካከላችሁ ባላችሁትና "አለንላችሁ" በሚሉን የክርስቶስ ቤተሰቦች ፍቅር ተጽናንተናል። እርሱ የሄደው ወደ ፈጠረው አምላክ ነውና ሐዘናችን በተስፋ የተሞላ ነው።
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሕይወት ታሪክ
ውልደትና የልጅነት ዘመን
መምህር ዘላለም ወንድሙ (ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት) ከአባታቸው ከአቶ ወንድሙ ተማም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ትክክልወርቅ ገብረኢየሱስ ነሐሴ 17 ቀን 1969 ዓ.ም በታሪካዊቷ ደብረ ሲና ከተማ ተወለደ። ገና በለጋነቱ የቤተክርስቲያንን ጠረን እየሳበ፣ በየኔት ታመነ እግር ሥር ተቀምጦ የቄስ ትምህርቱን በመቅሰም ለወደፊቱ መንፈሳዊ ተጋድሎው መሠረት ጣለ።
የትምህርት ጉብዝና እና የቅንነት መገለጫ
በትምህርቱ እጅግ ብሩህ የነበረው ዘላለም፣ በሰበታ ከተማ በነበረው የትምህርት ቆይታው ሁልጊዜም ከአንደኛነት አይወርድም ነበር። በተለይም በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች 100% በማምጣት አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
የሚገርመው ግን ዕውቀቱ ለራሱ ብቻ አልነበረም፤ ለሒሳብ ትምህርት የነበረው ልዩ ተሰጥኦ መምህራኑ በማይኖሩበት ጊዜ እርሱ መምህር ሆኖ ጓደኞቹን ያስተምር ነበር። ይህ "ሌሎችን የማብቃት" መልካም ባሕሪው ገና በልጅነቱ አብሮት ያደገ ጸጋው ነበር።
ከአግሮ ቴክኒክ ወደ ወንጌል አገልግሎት
በወሊሶ አግሮ ቴክኒካል ትምህርት ቤት በኤሌክትሪሲቲ ሙያ በዲፕሎማ ቢመረቅም፣ የልቡ ጥሪ ግን የሰው ልጅን ነፍስ በወንጌል ኤሌክትሪክ ማብራት ነበር። በወሊሶ ቆይታው ከብጹዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እግር ሥር ሆኖ በሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎቱን ጀመረ። የ12ኛ ክፍል ውጤቱ ለከፍተኛ ኮሌጅ ቢያበቃውም፣ እርሱ ግን "የእግዚአብሔር መንግሥት ትቀድማለች" ብሎ ራሱን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት አሳልፎ ሰጠ።
የአገልግሎት አሻራዎች፡ ከከተማ እስከ ገጠር
መምህር ዘላለም "የከተማ ኑሮ ይመቸኛል" ብሎ የተቀመጠ አገልጋይ አልነበረም። እግሩ ወንጌል ባልደረሰባቸውና እርዳታ በሚሹ አካባቢዎች ሁሉ ደርሷል፦
በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ስፍራዎች፡ ለማሌ፣ ሰሜን አሪ እና በና ፀማይ ብሔረሰቦች አምስት አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ የቃለ ወንጌል ብርሃን እንዲበራ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ የሌላ እምነት መሪዎችን አስተምሮ በማስጠመቅ አዳራሻቸውን ወደ ቤተክርስቲያንነት እንዲቀየር አድርጓል።
ለቋንቋ ተናጋሪዎች የሰጠው ትኩረት፡ በ2003 ዓ.ም ከ38 ልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተውጣጡ ደቀ መዛሙርትን አምጥቶ፣ ወጪያቸውን ሸፍኖ ካሰለጠነ በኋላ ወደየአካባቢያቸው እንዲያገለግሉ ልኮአቸዋል።
ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት፣የገዳማትና አድባራት አባቶች የሚሰጡትን ምስክርነት ሳያካትት ካከናወናቸው ዋና ዋና ሥራዎች፡
ደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት የከተማ አገልጋይ ብቻ አልነበረም፡፡ በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች ቃለ ወንጌልን በማስተማር ካበረከተው መንፈሳዊ አልግሎት በተጨማሪ፡
1. ለማሌ ብሔረሰብ -የማሌ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን
2. ለሰሜን አሪ ብሔረሰብ-የዘፍቲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
3. ለአሪ ብሔረሰብ-የሰልማ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን
4. ለበና ፀማይ ብሔረሰብ-የሙቃጫ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
5. የማላተር ቅዱስ ሚካኤል-በጅምር ላይ ያለ፡ በከተማው የነበሩትን ዋና ዋና ፓስተሮች
አስተምሮ በማስጠመቅ፣አዳራሻቸውን አፍርሰው ቆርቆሮውን በማምጣት
እንዲሠራ አድርገዋል፡፡
ጉሙዝ፣ጋምቤላ፣ጂንካ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት በ2003 ዓ.ም ከጠረፋማዋና ከገጠሪቱ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ 38 ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀ መዛሙርትን መልምሎና ከየሀገረ ስብከታቸው ማስረጃ አስጽፎ በማስመጣት ሙሉ የሥልጠና ወጪያቸውን በመሸፈን በጽርሐ ጽዮን የሥልጠና ማዕከል እንዲማሩ በማድረግ ሥልጠናቸውን ሲያጠናቅቁ፣ የአገልግ ሎት ልብስ እና መጽሐፍ ቅዱስ ገዝቶ በመስጠት ወደየመጡበት አካባቢ ተመልሰው በቋንቋቸ ው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
ጅጅጋ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም በጅጅጋ በደረሰው ችግር የተጎዱትን ለማጽናናት በሥፍራው ጉባኤ በማዘጋጀት ማኅበረ ምእመናንን ከማጽናናቱ በተጨማሪ ሰዎችን በማስተባበር ከ1,500,000.00 (ከአንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሽህ ብር) በላይ በማሰባሰብ በወቅቱ ለተጎዱ የሀገረ ስብከቱ ማኅበረ ካህናት ድጋፍ እንዲያገኙ በመርዳት የቤተክርስቲያን ልጅነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡
ሰበታ ቅዱስ ገብርኤል
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለ57 ዓይነ ስውራን በተለያዩ ጊዜያት ድጋፍ ከማድረጉ በተጨማሪ ለዘለቄታው ራሳቸውን የሚችሉበት ቦታ በመግዛት እንቅስቃሴ አስጀምሯል፡፡
በምሁር ኢየሱስ ገዳም
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት 12 ልጆችን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ በማስመጣት ዲቁና እንዲማሩና ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ-በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 2591 ሰዎች *3,000 ብር =7,773,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሸዋሮቢት፣አጣዬና ከሚሴ-ከተለያዩ አካባዎች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ድጋፍ አበርክቷል፡፡
ደብረ ዘይት-መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ከቢሾፍቱ ከተማ በቅርብ ከሚገኘውና የኢትዮጵያ አውሮፕላን ተከስክሶ ብዙ ሰው ባለቀበት ኤጄሬ ቦታ ላይ በአካል ተገኝቶ በማጽ ናናትና የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በማስፈቀድ የተለያዩ ሰዎችን በማስተባበር የቅድስት ልደታ ቤተክርስቲያንን አስተክሎ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአካል በመገኘት አስመርቋል፡፡
ቡታጅራ-በግጭት የተፈናቀሉትን ቦታው ድረስ ሄዶ በአካል በመገኘት በቃለ እግዚአብሔር ከማጽናናት በተጨማሪ የሚታወቅበትን መልካምነት በድጋፍ አሳይቷል፡፡
ከስልጤ ዞን ከቅበት ከተማ በክርስትናቸው ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ለ288 ሰዎች *2,000 ብር =576,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርሲ ሻሸመኔ ባሌ
ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉ እና ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች ሩዝ፣ዱቄት፣ዘይት እና የማሰያ ዕቃዎችን በማቅረብ መንፈሳዊ ኀላፊነታቸውን ተወጥቷል፡፡
አፋር
በአፋር ክልል ለሚገኙ በዞን 5 ሰሙሮቢ ወረዳ ኩማሜ አካባቢ -በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 495 ሰዎች* 3,000 ብር =1,485,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ስሙን "ማሩ!" በማለት የሚጠሩት የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሲኖዶስ አባ ብጹዕ አቡነ ዮናስ በስማቸው በዋሽ ዐርባ ለተቋቋመው አረጋውያን የጡረታ ማእከል የቦርድ ሰብሳቢ በመሆን እና በኀላፊነት በማገልገል ዓመታዊ የምግብ እገዛ አድርጓል፡፡
ደብረ ሊባኖስ ገዳም-ለአበው ካህናት ለአገልግሎት የሚሆን ልብሰ ተክህኖ ሰጥቷል
ደብረ ብርሃን-የአእምሮ ሕሙማን ማገገሚያ እንዲሆን በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማርያም ልጅ በተመሠረተው ሀበሻ የአረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ለንጽሕና መጠበቂያ የሚሆኑ ነገሮችን በማቅረብ ሃይማኖቱን በተግባር አስመስክሯል፡፡
ዋግህምራ ዞን ሰቆጣ- በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ901 ሰዎች *3,000 ብር =2,703,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ደባርቅ ወረዳ በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ294 ሰዎች *3,000 ብር =882,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ጎንደር-የአብነት ተማሪዎች ሲመረቁ ካባ ሰጥቷል፡፡
አዲስ አበባ
ይዲድያ መንፈሳዊ ማኅበር
እኁድ ከ 5፡00-7፡00 ሰዓት በቃለ እግዚአብሔር በሃይማኖት በምግባር እንዲጸኑ፣ እንዲያድጉና እንዲበረቱ ከማስተማር በተጨማሪ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለችግር የተጋላጡ ልጆችን በማስተማር ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ እስረኞች ለዳግም ትንሣኤ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ይዲድያ የሕፃናት መርጃ
ይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድርጅት በመምህር ዘላለም ወንድሙ መሥራችነትና አስባባሪነት በበጎ አድራጎት የተሰማራ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ ያለ ሃይማኖት፣ያለዘር፣ያለ ቋንቋ ልዩነት ወገናዊ ድጋፍ በማድረግ የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡ በይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድጋፍ ለሚደረግላቸው ልጆች ከ2008-2018 ባሉት ለ12 ዓመታት ከ2650 በላይ ለሆኑ ልጆች ከ15,000,000.00 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወገናዊ ደጋፉን በማድረግ ላይ የሚገኝ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን በአሁኑ ወቅት 200 ልጆችን በመርዳት ላይ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ በዝቅተኛ ኑሮ ለተቸገሩ 1000 ሰዎች 3,000 ብር =30,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
በየሳምንቱ ረቡዕና ዓርብ የሚደረግ የምሣ ምገባ
ሀ. ቂርቆስ 80 ልጆችን ፤ለ. ሣሪስ አቦ 148 ልጆችን፤ ሐ. የካ ሚካኤል 72 ልጆችን ባጠቃላይ ለ300 አቅመ ደካሞችን የምሣ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ለሚገኙ ጸበልተኞች ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
ወንጌለ ዘላለም ከተባለው የዩቲዩብ ቻናላቸው ከሚገኘው ገቢ፡
ግቢ ገብርኤል፣የወደቁትን አንሡ፣እንጦጦ ማርያም….ለሚገኙ ዐቅመ ደካሞች በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለአገልግሎት በሄዱበት በሀገረ አሜሪካ በገጠማቸው ድንገተኛ ሕመም የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፏል፡፡
የመምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በቅንነትና በታማኝነት ያገለገሉት አምላክ በአብርሃም፣በይስሐቅና በያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን፡፡ለኦርዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ለቤተሰቡ፣ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ያድልልን፡፡
✍️ “ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤”
በወንጌል አላፍርምና፤
አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም
ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ
የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14
እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን
ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በረሀብ በስደት ስላሉት እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት እንጸልይ
ስለ ሃይማኖት መሪዎች አባቶቻችን እንጸልይ
ስለ ሀገር መሪዎች እንጸልይ
የሰላም የምህረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምህረቱን ቸርነቱን አይንሳን
አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዘዝዋይ ገዳም
መጋቢት 3/7/2018 ✍️
ወንድም ተዋበ ወንድሙ እንዳነበበው
#ethiopia | የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ቤተሰቦችና የመምህር ዘላለም ወዳጆች፤ ዛሬ የምንናገረው ስለ አንድ ሥጋዊ ወንድማችን ብቻ አይደለም፤ የምንናገረው ስለ ብዙዎች አባት፣ ስለ ድሆች ረዳትና ስለ ወንጌል ብርሃን ነው። መምህር ዘላለምን በሥጋ መለየታችን ለአንጀታችን እጅግ የሚከብድ፣ ለቤተሰባችንም መሪር ሐዘን ቢሆንብንም፤ እርሱ ግን አስቀድሞ በመልካም ሥራው በሰማይ ቤት ቤቱን ሰርቶ እንደነበር እናምናለን።
ምንም እንኳን በሰውነታችን ብናዝንም፣ በብጹዓን አባቶቻችን ጸሎትና ትምህርት፣ እንዲሁም በዚህ በመካከላችሁ ባላችሁትና "አለንላችሁ" በሚሉን የክርስቶስ ቤተሰቦች ፍቅር ተጽናንተናል። እርሱ የሄደው ወደ ፈጠረው አምላክ ነውና ሐዘናችን በተስፋ የተሞላ ነው።
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሕይወት ታሪክ
ውልደትና የልጅነት ዘመን
መምህር ዘላለም ወንድሙ (ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት) ከአባታቸው ከአቶ ወንድሙ ተማም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ትክክልወርቅ ገብረኢየሱስ ነሐሴ 17 ቀን 1969 ዓ.ም በታሪካዊቷ ደብረ ሲና ከተማ ተወለደ። ገና በለጋነቱ የቤተክርስቲያንን ጠረን እየሳበ፣ በየኔት ታመነ እግር ሥር ተቀምጦ የቄስ ትምህርቱን በመቅሰም ለወደፊቱ መንፈሳዊ ተጋድሎው መሠረት ጣለ።
የትምህርት ጉብዝና እና የቅንነት መገለጫ
በትምህርቱ እጅግ ብሩህ የነበረው ዘላለም፣ በሰበታ ከተማ በነበረው የትምህርት ቆይታው ሁልጊዜም ከአንደኛነት አይወርድም ነበር። በተለይም በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች 100% በማምጣት አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
የሚገርመው ግን ዕውቀቱ ለራሱ ብቻ አልነበረም፤ ለሒሳብ ትምህርት የነበረው ልዩ ተሰጥኦ መምህራኑ በማይኖሩበት ጊዜ እርሱ መምህር ሆኖ ጓደኞቹን ያስተምር ነበር። ይህ "ሌሎችን የማብቃት" መልካም ባሕሪው ገና በልጅነቱ አብሮት ያደገ ጸጋው ነበር።
ከአግሮ ቴክኒክ ወደ ወንጌል አገልግሎት
በወሊሶ አግሮ ቴክኒካል ትምህርት ቤት በኤሌክትሪሲቲ ሙያ በዲፕሎማ ቢመረቅም፣ የልቡ ጥሪ ግን የሰው ልጅን ነፍስ በወንጌል ኤሌክትሪክ ማብራት ነበር። በወሊሶ ቆይታው ከብጹዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እግር ሥር ሆኖ በሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎቱን ጀመረ። የ12ኛ ክፍል ውጤቱ ለከፍተኛ ኮሌጅ ቢያበቃውም፣ እርሱ ግን "የእግዚአብሔር መንግሥት ትቀድማለች" ብሎ ራሱን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት አሳልፎ ሰጠ።
የአገልግሎት አሻራዎች፡ ከከተማ እስከ ገጠር
መምህር ዘላለም "የከተማ ኑሮ ይመቸኛል" ብሎ የተቀመጠ አገልጋይ አልነበረም። እግሩ ወንጌል ባልደረሰባቸውና እርዳታ በሚሹ አካባቢዎች ሁሉ ደርሷል፦
በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ስፍራዎች፡ ለማሌ፣ ሰሜን አሪ እና በና ፀማይ ብሔረሰቦች አምስት አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ የቃለ ወንጌል ብርሃን እንዲበራ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ የሌላ እምነት መሪዎችን አስተምሮ በማስጠመቅ አዳራሻቸውን ወደ ቤተክርስቲያንነት እንዲቀየር አድርጓል።
ለቋንቋ ተናጋሪዎች የሰጠው ትኩረት፡ በ2003 ዓ.ም ከ38 ልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተውጣጡ ደቀ መዛሙርትን አምጥቶ፣ ወጪያቸውን ሸፍኖ ካሰለጠነ በኋላ ወደየአካባቢያቸው እንዲያገለግሉ ልኮአቸዋል።
ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት፣የገዳማትና አድባራት አባቶች የሚሰጡትን ምስክርነት ሳያካትት ካከናወናቸው ዋና ዋና ሥራዎች፡
ደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት የከተማ አገልጋይ ብቻ አልነበረም፡፡ በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች ቃለ ወንጌልን በማስተማር ካበረከተው መንፈሳዊ አልግሎት በተጨማሪ፡
1. ለማሌ ብሔረሰብ -የማሌ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን
2. ለሰሜን አሪ ብሔረሰብ-የዘፍቲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
3. ለአሪ ብሔረሰብ-የሰልማ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን
4. ለበና ፀማይ ብሔረሰብ-የሙቃጫ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
5. የማላተር ቅዱስ ሚካኤል-በጅምር ላይ ያለ፡ በከተማው የነበሩትን ዋና ዋና ፓስተሮች
አስተምሮ በማስጠመቅ፣አዳራሻቸውን አፍርሰው ቆርቆሮውን በማምጣት
እንዲሠራ አድርገዋል፡፡
ጉሙዝ፣ጋምቤላ፣ጂንካ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት በ2003 ዓ.ም ከጠረፋማዋና ከገጠሪቱ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ 38 ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀ መዛሙርትን መልምሎና ከየሀገረ ስብከታቸው ማስረጃ አስጽፎ በማስመጣት ሙሉ የሥልጠና ወጪያቸውን በመሸፈን በጽርሐ ጽዮን የሥልጠና ማዕከል እንዲማሩ በማድረግ ሥልጠናቸውን ሲያጠናቅቁ፣ የአገልግ ሎት ልብስ እና መጽሐፍ ቅዱስ ገዝቶ በመስጠት ወደየመጡበት አካባቢ ተመልሰው በቋንቋቸ ው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
ጅጅጋ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም በጅጅጋ በደረሰው ችግር የተጎዱትን ለማጽናናት በሥፍራው ጉባኤ በማዘጋጀት ማኅበረ ምእመናንን ከማጽናናቱ በተጨማሪ ሰዎችን በማስተባበር ከ1,500,000.00 (ከአንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሽህ ብር) በላይ በማሰባሰብ በወቅቱ ለተጎዱ የሀገረ ስብከቱ ማኅበረ ካህናት ድጋፍ እንዲያገኙ በመርዳት የቤተክርስቲያን ልጅነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡
ሰበታ ቅዱስ ገብርኤል
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለ57 ዓይነ ስውራን በተለያዩ ጊዜያት ድጋፍ ከማድረጉ በተጨማሪ ለዘለቄታው ራሳቸውን የሚችሉበት ቦታ በመግዛት እንቅስቃሴ አስጀምሯል፡፡
በምሁር ኢየሱስ ገዳም
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት 12 ልጆችን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ በማስመጣት ዲቁና እንዲማሩና ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ-በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 2591 ሰዎች *3,000 ብር =7,773,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሸዋሮቢት፣አጣዬና ከሚሴ-ከተለያዩ አካባዎች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ድጋፍ አበርክቷል፡፡
ደብረ ዘይት-መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ከቢሾፍቱ ከተማ በቅርብ ከሚገኘውና የኢትዮጵያ አውሮፕላን ተከስክሶ ብዙ ሰው ባለቀበት ኤጄሬ ቦታ ላይ በአካል ተገኝቶ በማጽ ናናትና የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በማስፈቀድ የተለያዩ ሰዎችን በማስተባበር የቅድስት ልደታ ቤተክርስቲያንን አስተክሎ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአካል በመገኘት አስመርቋል፡፡
ቡታጅራ-በግጭት የተፈናቀሉትን ቦታው ድረስ ሄዶ በአካል በመገኘት በቃለ እግዚአብሔር ከማጽናናት በተጨማሪ የሚታወቅበትን መልካምነት በድጋፍ አሳይቷል፡፡
ከስልጤ ዞን ከቅበት ከተማ በክርስትናቸው ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ለ288 ሰዎች *2,000 ብር =576,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርሲ ሻሸመኔ ባሌ
ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉ እና ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች ሩዝ፣ዱቄት፣ዘይት እና የማሰያ ዕቃዎችን በማቅረብ መንፈሳዊ ኀላፊነታቸውን ተወጥቷል፡፡
አፋር
በአፋር ክልል ለሚገኙ በዞን 5 ሰሙሮቢ ወረዳ ኩማሜ አካባቢ -በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 495 ሰዎች* 3,000 ብር =1,485,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ስሙን "ማሩ!" በማለት የሚጠሩት የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሲኖዶስ አባ ብጹዕ አቡነ ዮናስ በስማቸው በዋሽ ዐርባ ለተቋቋመው አረጋውያን የጡረታ ማእከል የቦርድ ሰብሳቢ በመሆን እና በኀላፊነት በማገልገል ዓመታዊ የምግብ እገዛ አድርጓል፡፡
ደብረ ሊባኖስ ገዳም-ለአበው ካህናት ለአገልግሎት የሚሆን ልብሰ ተክህኖ ሰጥቷል
ደብረ ብርሃን-የአእምሮ ሕሙማን ማገገሚያ እንዲሆን በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማርያም ልጅ በተመሠረተው ሀበሻ የአረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ለንጽሕና መጠበቂያ የሚሆኑ ነገሮችን በማቅረብ ሃይማኖቱን በተግባር አስመስክሯል፡፡
ዋግህምራ ዞን ሰቆጣ- በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ901 ሰዎች *3,000 ብር =2,703,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ደባርቅ ወረዳ በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ294 ሰዎች *3,000 ብር =882,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ጎንደር-የአብነት ተማሪዎች ሲመረቁ ካባ ሰጥቷል፡፡
አዲስ አበባ
ይዲድያ መንፈሳዊ ማኅበር
እኁድ ከ 5፡00-7፡00 ሰዓት በቃለ እግዚአብሔር በሃይማኖት በምግባር እንዲጸኑ፣ እንዲያድጉና እንዲበረቱ ከማስተማር በተጨማሪ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለችግር የተጋላጡ ልጆችን በማስተማር ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ እስረኞች ለዳግም ትንሣኤ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ይዲድያ የሕፃናት መርጃ
ይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድርጅት በመምህር ዘላለም ወንድሙ መሥራችነትና አስባባሪነት በበጎ አድራጎት የተሰማራ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ ያለ ሃይማኖት፣ያለዘር፣ያለ ቋንቋ ልዩነት ወገናዊ ድጋፍ በማድረግ የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡ በይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድጋፍ ለሚደረግላቸው ልጆች ከ2008-2018 ባሉት ለ12 ዓመታት ከ2650 በላይ ለሆኑ ልጆች ከ15,000,000.00 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወገናዊ ደጋፉን በማድረግ ላይ የሚገኝ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን በአሁኑ ወቅት 200 ልጆችን በመርዳት ላይ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ በዝቅተኛ ኑሮ ለተቸገሩ 1000 ሰዎች 3,000 ብር =30,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
በየሳምንቱ ረቡዕና ዓርብ የሚደረግ የምሣ ምገባ
ሀ. ቂርቆስ 80 ልጆችን ፤ለ. ሣሪስ አቦ 148 ልጆችን፤ ሐ. የካ ሚካኤል 72 ልጆችን ባጠቃላይ ለ300 አቅመ ደካሞችን የምሣ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ለሚገኙ ጸበልተኞች ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
ወንጌለ ዘላለም ከተባለው የዩቲዩብ ቻናላቸው ከሚገኘው ገቢ፡
ግቢ ገብርኤል፣የወደቁትን አንሡ፣እንጦጦ ማርያም….ለሚገኙ ዐቅመ ደካሞች በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለአገልግሎት በሄዱበት በሀገረ አሜሪካ በገጠማቸው ድንገተኛ ሕመም የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፏል፡፡
የመምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በቅንነትና በታማኝነት ያገለገሉት አምላክ በአብርሃም፣በይስሐቅና በያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን፡፡ለኦርዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ለቤተሰቡ፣ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ያድልልን፡፡
✍️ “ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤”
በወንጌል አላፍርምና፤
አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም
ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ
የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14
እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን
ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በረሀብ በስደት ስላሉት እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት እንጸልይ
ስለ ሃይማኖት መሪዎች አባቶቻችን እንጸልይ
ስለ ሀገር መሪዎች እንጸልይ
የሰላም የምህረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምህረቱን ቸርነቱን አይንሳን
አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዘዝዋይ ገዳም
መጋቢት 3/7/2018 ✍️
4 months ago
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ የኃዘን መግለጫ
‹‹እለ ሐሙ በእንተ ስሙ፤ ምድር ሠናይት ርስቶሙ
ስለስሙ መከራን የተቀበሉት፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናት››
(ማቴ 5÷51 ፤ ቅዱስ ያሬድ)
ከዚህ በፊት በአርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች የበርካታ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሕይወት በመጥፋቱና ከሞት የተረፉትም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞች ተሰደው ለረሀብና ለእርዛት ተጋልጠው እየኖሩ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ቀደም ሲል በተለያዩ ጊዜያት፣ በደረሰው ሞትና ስደት ምእመናን እያዘነ ባሉበት፣ እኛም ከኃዘናችን ባልተጽናናንበት ሁኔታ ጥቃቱ በአዲስ መልኩ ቀጥሎ የ21 ንጹሐን ወገኖቻችን ሕይወት በግፍ ማለፉን፣ በሕይወት የተረፉትም በታጣቂዎቹ መታገታቸውንና የደረሱበት አለመታወቁን፣ h10 የሚበልጡ አባውራዎች ቤትና ንብረት እንደተቃጠለ በመግለጽ ከሀገረ ስብከቱ የቀረበውን ሪፖርት የተመለከትነው ጥልቅ በሆነ ኃዘን ነው፡፡
አገር ሰላም ብለው በሚኖሩት ከምንም ጉዳይ ጋር ንክኪ በሌላቸው ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን ላይ ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላትም ግድያውን በሃይማኖት ስም ይፈጽሙት እንጂ የሃይማኖት ስዎች ግን አይደሉም፡፡ ዓላማቸውም በሀገራችን ለረዥም ዘመናት ተከባብረው አብረው በኖሩት የሃይማኖት ተቋማት መካከል ግጭትን መፍጠር ነውና የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና ሕዝበ ክርስቲያኑ በጋራ ልናወግዛቸው ይገባል፡፡
በመሆኑም በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ በሕዝበ ክርስቲያኑ ዕለታዊ ኑሮ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር፣ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ በሰው ልጅ ሰብአዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው አጸያፊ ድርጊት በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ አውግዞታል፡፡
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለው ሞትና መፈናቀልም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን በየትኛውም የሀገራችን ክፍል በነጻነት ሠርተው የመኖርና ሥርዓተ አምልኮ የመፈጸም ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጋፋ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ተከታትለው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡበት ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፣
ፍርድን በመሻት የሚጮኸው ስለስሙ መከራን የተቀበሉት የንጹሐን ደም ተገቢውን ፍትሕ ይፈልጋልና ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ፣ ወደፊትም ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት እንዳይጠፋ፣ የዜጐች ሀብትና ንብረት እንዳይወድም መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ተግባሩን እንዲያከናውን ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን በአጽንኦት ያስተላልፋል፤
በደረሰው አደጋ ዙሪያ ተነጋግሮ ተገቢውን ውሳኔ ለማስተላለፍ የተሰበሰበው ቋሚ ሲኖዶስም የአካባቢው ችግር አስተማማኝ በሆነ መንገድ ተፈትቶ ዘላቂ ስላም እስኪገኝ ድረስ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተሰየመው የሀገር ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ዐቢይ ኮሚቴ ከፌደራልና ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና የሚመለከታቸውም አካላት በየድርሻቸው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ በክብር ያሳስባል፡፡
የክልሉ መንግሥትና የአካባቢው መስተዳድርም ችግሩን ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥልና ወደፊትም ችግሩ እንዳይደገም ከመሠረቱ መፍታት የሚያስችል እርምጃ እንዲወስድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትጠይቃለች፡፡
በመጨረሻም ስለስሙ በሥጋቸው መከራን በመቀበል ሕይወታቸውን በአጡት ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን የተሰማንን መሪር ኃዘን እየገለጽን ልዑል እግዚአብሔር ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጥልን፣ ቤተሰቦቻቸውንም እንዲያጽናናልን እንጸልያለን፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ
የካቲት 2018 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
‹‹እለ ሐሙ በእንተ ስሙ፤ ምድር ሠናይት ርስቶሙ
ስለስሙ መከራን የተቀበሉት፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናት››
(ማቴ 5÷51 ፤ ቅዱስ ያሬድ)
ከዚህ በፊት በአርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች የበርካታ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሕይወት በመጥፋቱና ከሞት የተረፉትም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞች ተሰደው ለረሀብና ለእርዛት ተጋልጠው እየኖሩ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ቀደም ሲል በተለያዩ ጊዜያት፣ በደረሰው ሞትና ስደት ምእመናን እያዘነ ባሉበት፣ እኛም ከኃዘናችን ባልተጽናናንበት ሁኔታ ጥቃቱ በአዲስ መልኩ ቀጥሎ የ21 ንጹሐን ወገኖቻችን ሕይወት በግፍ ማለፉን፣ በሕይወት የተረፉትም በታጣቂዎቹ መታገታቸውንና የደረሱበት አለመታወቁን፣ h10 የሚበልጡ አባውራዎች ቤትና ንብረት እንደተቃጠለ በመግለጽ ከሀገረ ስብከቱ የቀረበውን ሪፖርት የተመለከትነው ጥልቅ በሆነ ኃዘን ነው፡፡
አገር ሰላም ብለው በሚኖሩት ከምንም ጉዳይ ጋር ንክኪ በሌላቸው ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን ላይ ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላትም ግድያውን በሃይማኖት ስም ይፈጽሙት እንጂ የሃይማኖት ስዎች ግን አይደሉም፡፡ ዓላማቸውም በሀገራችን ለረዥም ዘመናት ተከባብረው አብረው በኖሩት የሃይማኖት ተቋማት መካከል ግጭትን መፍጠር ነውና የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና ሕዝበ ክርስቲያኑ በጋራ ልናወግዛቸው ይገባል፡፡
በመሆኑም በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ በሕዝበ ክርስቲያኑ ዕለታዊ ኑሮ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር፣ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ በሰው ልጅ ሰብአዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው አጸያፊ ድርጊት በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ አውግዞታል፡፡
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለው ሞትና መፈናቀልም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን በየትኛውም የሀገራችን ክፍል በነጻነት ሠርተው የመኖርና ሥርዓተ አምልኮ የመፈጸም ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጋፋ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ተከታትለው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡበት ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፣
ፍርድን በመሻት የሚጮኸው ስለስሙ መከራን የተቀበሉት የንጹሐን ደም ተገቢውን ፍትሕ ይፈልጋልና ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ፣ ወደፊትም ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት እንዳይጠፋ፣ የዜጐች ሀብትና ንብረት እንዳይወድም መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ተግባሩን እንዲያከናውን ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን በአጽንኦት ያስተላልፋል፤
በደረሰው አደጋ ዙሪያ ተነጋግሮ ተገቢውን ውሳኔ ለማስተላለፍ የተሰበሰበው ቋሚ ሲኖዶስም የአካባቢው ችግር አስተማማኝ በሆነ መንገድ ተፈትቶ ዘላቂ ስላም እስኪገኝ ድረስ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተሰየመው የሀገር ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ዐቢይ ኮሚቴ ከፌደራልና ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና የሚመለከታቸውም አካላት በየድርሻቸው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ በክብር ያሳስባል፡፡
የክልሉ መንግሥትና የአካባቢው መስተዳድርም ችግሩን ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥልና ወደፊትም ችግሩ እንዳይደገም ከመሠረቱ መፍታት የሚያስችል እርምጃ እንዲወስድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትጠይቃለች፡፡
በመጨረሻም ስለስሙ በሥጋቸው መከራን በመቀበል ሕይወታቸውን በአጡት ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን የተሰማንን መሪር ኃዘን እየገለጽን ልዑል እግዚአብሔር ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጥልን፣ ቤተሰቦቻቸውንም እንዲያጽናናልን እንጸልያለን፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ
የካቲት 2018 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
4 months ago
#በእንተ - ግርማ!
#ethiopia | በግርማ ሙዚቃዎች ውስጥ ሁሉ ያለችው ሴት አንድ ናት፡ ፡የሚወዳት የሚያኮርፋት፣ የሚቀርባት የሚርቃት እሷን ብቻ ነው-እጸገነትን፡፡ እጸገነት ገብረሥላሴ የልጅነቱ ናት፤ የልጁም እናት፡፡ በንጹሕ ልቡ የወደዳት፤ የምትወደው፡፡ “ሴት አላምንም” ፣ “ትወጅኝ እንደሁ”፣"ቁርጡን ንገሪኝ"እና “ፍቅር እንደክራር”ብሎ ያዜመላት፡፡ “ይበቃናል” ብሎ ያንጎራጎረውም ለእጸገነት ነው- የራቀችው ቢመስለው፡፡ ግን አይሆንለትም፡፡"ጥሩልኝ ቶሎ" ይላል፡፡
አቃተኝ ፍፁም መለየት
እሷን ከመሰለ ወጣት
ጥሩልኝ ቶሎ በፍጥነት
ትድረስ በነፍሴ ሳልሞት
ፍፁም ፍፁም አልተዋትም
ካለሁ በሕይወት አረሳትም...
"ጥሩልኝ ቶሎ" የግርማ የአፍላነት ዜማ ነበር፡፡ ኋላ ግን የአሳዛኝ ሕይወቱ ማጀቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ በፍቅራቸው ሰሞን ስትጠፋበት "ጥሩልኝ ቶሎ"ብሎ ያንጎራጎረላት እጸገነት በጎልማሳነቱ ዘመን ጥላው ሔደች-ወደ አምላኳ፡፡ ግርማ ከእዚያ በኋላ ሙዚቃን ፈራ፡፡ በብዙ ጉትጎታ ተመልሶ ሲመጣም ከእጸገነት መራቅ ተሳነው፡፡ “Mistakes on purpose” ብሎ በሰየመው የሙዚቃ አልበሙ ላይም “በመልክሽ አይደለም” በተሰኘ ዜማው የልጅነት ፍቅሩን ዘከረ፡፡ በካንሰር ሕመም ካለፈች 32 ዓመታት ቢሞላትም ዛሬም ፎቶዋን አቅፎ እንደሚተኛ አንጎራጎረ፡፡
እስኪመሽ እናፍቃለሁ፤ እስክተኛም እጓጓለሁ ምክንያቱም ጸጊን ስለማገኛት አለ፡፡ ግርማ ዕድሜውን ሙሉ የዘፈነላት ሴት አሁንም አብራው እንዳለች ያስባል፡፡ በጊዜ ቤቱ ገብቶ ከፎቶዋ ጋር ሲጫወት ያመሻል፡፡ እኔም ተራው ደርሶኝ በድጋሚ እስካገኛት እያለ ፡፡...!
#በቅርብ በድጋሚ ለንባብ ከበቃው #ጠመንጃና ሙዚቃ መጽሐፍ የተወሰደ፤
ጠመንጃና ሙዚቃ ምን ይዟል?
1- የኢትዮጵያን ፖለቲካና ሙዚቃ ታሪክ በስፋት ተርኳል
2- ከአንድ ሺህ በላይ የግጥም፣ የዜማና የቅንብር ሥራዎችን መረጃዎች በዝርዝር አቅርቧል
3-አርባ ያህል የሙዚቃ ሰዎችን የሕይወት ታሪክ አካቷል
4-የኢትዮጵያን ማኅበራዊ ታሪክ በስፋት መርምሯል
በጃፋር መጽሐፍት ያገኙታል
#ethiopia | በግርማ ሙዚቃዎች ውስጥ ሁሉ ያለችው ሴት አንድ ናት፡ ፡የሚወዳት የሚያኮርፋት፣ የሚቀርባት የሚርቃት እሷን ብቻ ነው-እጸገነትን፡፡ እጸገነት ገብረሥላሴ የልጅነቱ ናት፤ የልጁም እናት፡፡ በንጹሕ ልቡ የወደዳት፤ የምትወደው፡፡ “ሴት አላምንም” ፣ “ትወጅኝ እንደሁ”፣"ቁርጡን ንገሪኝ"እና “ፍቅር እንደክራር”ብሎ ያዜመላት፡፡ “ይበቃናል” ብሎ ያንጎራጎረውም ለእጸገነት ነው- የራቀችው ቢመስለው፡፡ ግን አይሆንለትም፡፡"ጥሩልኝ ቶሎ" ይላል፡፡
አቃተኝ ፍፁም መለየት
እሷን ከመሰለ ወጣት
ጥሩልኝ ቶሎ በፍጥነት
ትድረስ በነፍሴ ሳልሞት
ፍፁም ፍፁም አልተዋትም
ካለሁ በሕይወት አረሳትም...
"ጥሩልኝ ቶሎ" የግርማ የአፍላነት ዜማ ነበር፡፡ ኋላ ግን የአሳዛኝ ሕይወቱ ማጀቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ በፍቅራቸው ሰሞን ስትጠፋበት "ጥሩልኝ ቶሎ"ብሎ ያንጎራጎረላት እጸገነት በጎልማሳነቱ ዘመን ጥላው ሔደች-ወደ አምላኳ፡፡ ግርማ ከእዚያ በኋላ ሙዚቃን ፈራ፡፡ በብዙ ጉትጎታ ተመልሶ ሲመጣም ከእጸገነት መራቅ ተሳነው፡፡ “Mistakes on purpose” ብሎ በሰየመው የሙዚቃ አልበሙ ላይም “በመልክሽ አይደለም” በተሰኘ ዜማው የልጅነት ፍቅሩን ዘከረ፡፡ በካንሰር ሕመም ካለፈች 32 ዓመታት ቢሞላትም ዛሬም ፎቶዋን አቅፎ እንደሚተኛ አንጎራጎረ፡፡
እስኪመሽ እናፍቃለሁ፤ እስክተኛም እጓጓለሁ ምክንያቱም ጸጊን ስለማገኛት አለ፡፡ ግርማ ዕድሜውን ሙሉ የዘፈነላት ሴት አሁንም አብራው እንዳለች ያስባል፡፡ በጊዜ ቤቱ ገብቶ ከፎቶዋ ጋር ሲጫወት ያመሻል፡፡ እኔም ተራው ደርሶኝ በድጋሚ እስካገኛት እያለ ፡፡...!
#በቅርብ በድጋሚ ለንባብ ከበቃው #ጠመንጃና ሙዚቃ መጽሐፍ የተወሰደ፤
ጠመንጃና ሙዚቃ ምን ይዟል?
1- የኢትዮጵያን ፖለቲካና ሙዚቃ ታሪክ በስፋት ተርኳል
2- ከአንድ ሺህ በላይ የግጥም፣ የዜማና የቅንብር ሥራዎችን መረጃዎች በዝርዝር አቅርቧል
3-አርባ ያህል የሙዚቃ ሰዎችን የሕይወት ታሪክ አካቷል
4-የኢትዮጵያን ማኅበራዊ ታሪክ በስፋት መርምሯል
በጃፋር መጽሐፍት ያገኙታል
8 months ago
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ አባቶች፣ ካህናትና ምዕመናን የሰላም ጥሪ አቀረበ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣
የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣
በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣
የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣
በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
8 months ago
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣
የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣
በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣
የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣
በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡
በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
8 months ago
ቅዱስ ሲኖዶስ ለትግራይ አባቶች፣ ካህናትና ምዕመናን የሰላም ጥሪ አቀረበ
***
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
***
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
“ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ …
የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡
ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል
በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡
ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣
ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣
መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ
ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤
በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣
መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤
8 months ago
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ፓትያርክ አባ ማትያስ ቀዳማዊ በዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በሀገሪቱ የሚታየው የእርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።
በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጎዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡
ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡
የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ብለዋል።
(የቅዱስ ፓትያርኩ ሙሉ መልዕክት ከዚህ በታች ቀርቧል)
***
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
• ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤
የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡
“ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬)
ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡
እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በጐዶሎው ዓለም የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ጉድለቷን ለመሙላት ብዙ መሥዋዕትነት ከፍላለች፤ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣዩ ትውልድ መሸጋገርና የጐደለባትን ለመሙላት ስትል ከቅዱሳን ሐዋርያት አንሥቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙና የብዙ ብዙ አበው ካህናትን፣ ሊቃውንትንና ምእመናንን ከደም ጠብታ፣ እስከ ቁስ ስጦታ ገብራለች፡፡
አሁን በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሁሉ ውጤት ናት፤ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ ዛሬም የጐደለባት ብዙ ነገር አለ፤ በተቻለ መጠን እርሱን ለሟሟላት መጣርና በተሻለ ሁኔታ ወደፊት ማሻገር ደግሞ የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ጉባኤ ብቻው አይደለም፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ የእግዚአብሔር ልጆች ድምፁን ለመስማት ከዙሪያው ሆነው በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ እነኝህ የእግዚአብሔር ልጆች ለመስማት ብቻ ሳይሆን ድምፁን ሰምተው ለመታዘዝም የተዘጋጁ ናቸው፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ “ሁለትም ሦስትም ሆናችሁ በስሜ በተሰበሰባችሁበት እኔ በመካከላችሁ እገኛለሁ” በማለት ጉባኤውን የመሠረተው አምላክ ከዚህ ጉባኤ መካከል አለ፡፡
በመሆኑም ይህ ጉባኤ የተወሰን አባቶች ብቻ ሳንሆን ብዙ ሰማውያንና ምድራውያን ባለድርሻ ያሉበት፣ መንፈስ ቅዱስም በመንፈስ የሚመራው እንደሆነ የማይታበል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው በምድር ያለችውን የእግዚአብሔር መንግሥት በበላይነት የሚመራ ነውና፣ ያለበት ኃላፊነት ከባድና እጅግ የላቀ ነው፡፡ ጉባኤው ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ የሚሰጠው ሽልማት ታላቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ኃላፊነቱን በትክክል ካልተወጣ ደግሞ ተጠያቂነቱ በዚያው ልክ ከባድ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለጋል ተብሎአልና፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
እኛ በአገልግሎትና በመሪነት በምንገኝበት በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጐደሉባት ነገሮች ብዙ ናቸው፤ ከሁሉ በላይ በውስጣችን የአንድነት ጐድለት በስፋት ይታያል፤ ለተሰየምንለት መለኮታዊ ተልእኮ አንድ ሐሳብ፣ አንድ ቃል፣ አንድ ልብ ሆነን መሰለፍ ያለመቻል ክፍተት እየተንጸባረቀ ነው፡፡ የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው፡፡ በእነዚህ ዓበይት ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ጉድለቶቻች ላይ ፈጣን፣ ቈራጥና አዋጭ የሆነ ሥራ ካልሰራን ለወደፊት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ጥያቄ ውስጥ መክተቱ አይቀሬ ነው፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ቤተ ክርስቲያናችን በተጠቀሱት ችግሮች ተከባ ባለችበት ሁኔታ የሀገራችን ሰላም መቀዛቀዝ ደግሞ ሌላው ተጨማሪ ጉድለትን እያስከተለብን ነው፡፡ አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡ ይኽም ሁሉ ሆኖ ፍትሕን እያገኙ አይደለም፤ አብያተ ክርስቲያናትም በምእመናን ፍልሰት እየተዘጉም እየተቃጠሉም ነው፡፡
ከዚህም ሌላ የሌለን ነገር እንዳለ አስመስሎ ከየአቅጣጫው የሚወረወረው የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል፤ በቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ላይ በዓላማ የተነሡ አካላት የላኳቸው እንዳሉ በሚመስል መልኩ በስመ ተሐድሶ የሚደረገው እንቅስቃሴ የኛው መለያ የሆነውን ንዋየ ቅድሳትና ልብሰ ተክህኖ፣ መዝሙርና ሥርዓተ አምልኮ በመጠቀም ቤተ ክርስቲያናችንን በአደባባይ እየተዳፈረ ይገኛል፡፡
ይህ አላስፈላጊ ተግባር የሀገሪቱን ዜጎች በእኩልነት የሚያስተዳድረውን ሕገ መንግሥት በቀጥታ የሚፃረር ድርጊት ነው፤ ሆኖም በሕግ የሚጠይቅና የሚያስቆም አካል አልተገኘም፤ እኛም ዝምታን የመረጥን መስለናል፡፡ ነገር ግን መፍትሔው ዝምታ ሳይሆን በሕግ አግባብ ነገሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በዘመናችን እየተከሠተ ያለው ችግር ስንዘረዝር ውለን ብናድር መናገሩ በራሱ መፍትሔ ሊያመጣልን አይችልም፤ ጉባኤው ከዚህ በላይ መናገር እንደሚችልም እንገነዘባለን፤ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ የሚችል መደላድል ይህ ጉባኤ በዚህ ስብሰባ ሊተልም ይገባል ብለን ከአደራ ጋር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ
በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጎዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡
ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡
የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ብለዋል።
(የቅዱስ ፓትያርኩ ሙሉ መልዕክት ከዚህ በታች ቀርቧል)
***
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
• ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
• ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤
የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡
“ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬)
ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡
እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በጐዶሎው ዓለም የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ጉድለቷን ለመሙላት ብዙ መሥዋዕትነት ከፍላለች፤ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣዩ ትውልድ መሸጋገርና የጐደለባትን ለመሙላት ስትል ከቅዱሳን ሐዋርያት አንሥቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙና የብዙ ብዙ አበው ካህናትን፣ ሊቃውንትንና ምእመናንን ከደም ጠብታ፣ እስከ ቁስ ስጦታ ገብራለች፡፡
አሁን በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሁሉ ውጤት ናት፤ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ ዛሬም የጐደለባት ብዙ ነገር አለ፤ በተቻለ መጠን እርሱን ለሟሟላት መጣርና በተሻለ ሁኔታ ወደፊት ማሻገር ደግሞ የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ጉባኤ ብቻው አይደለም፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ የእግዚአብሔር ልጆች ድምፁን ለመስማት ከዙሪያው ሆነው በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ እነኝህ የእግዚአብሔር ልጆች ለመስማት ብቻ ሳይሆን ድምፁን ሰምተው ለመታዘዝም የተዘጋጁ ናቸው፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ “ሁለትም ሦስትም ሆናችሁ በስሜ በተሰበሰባችሁበት እኔ በመካከላችሁ እገኛለሁ” በማለት ጉባኤውን የመሠረተው አምላክ ከዚህ ጉባኤ መካከል አለ፡፡
በመሆኑም ይህ ጉባኤ የተወሰን አባቶች ብቻ ሳንሆን ብዙ ሰማውያንና ምድራውያን ባለድርሻ ያሉበት፣ መንፈስ ቅዱስም በመንፈስ የሚመራው እንደሆነ የማይታበል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው በምድር ያለችውን የእግዚአብሔር መንግሥት በበላይነት የሚመራ ነውና፣ ያለበት ኃላፊነት ከባድና እጅግ የላቀ ነው፡፡ ጉባኤው ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ የሚሰጠው ሽልማት ታላቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ኃላፊነቱን በትክክል ካልተወጣ ደግሞ ተጠያቂነቱ በዚያው ልክ ከባድ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለጋል ተብሎአልና፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
እኛ በአገልግሎትና በመሪነት በምንገኝበት በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጐደሉባት ነገሮች ብዙ ናቸው፤ ከሁሉ በላይ በውስጣችን የአንድነት ጐድለት በስፋት ይታያል፤ ለተሰየምንለት መለኮታዊ ተልእኮ አንድ ሐሳብ፣ አንድ ቃል፣ አንድ ልብ ሆነን መሰለፍ ያለመቻል ክፍተት እየተንጸባረቀ ነው፡፡ የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው፡፡ በእነዚህ ዓበይት ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ጉድለቶቻች ላይ ፈጣን፣ ቈራጥና አዋጭ የሆነ ሥራ ካልሰራን ለወደፊት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ጥያቄ ውስጥ መክተቱ አይቀሬ ነው፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ቤተ ክርስቲያናችን በተጠቀሱት ችግሮች ተከባ ባለችበት ሁኔታ የሀገራችን ሰላም መቀዛቀዝ ደግሞ ሌላው ተጨማሪ ጉድለትን እያስከተለብን ነው፡፡ አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡ ይኽም ሁሉ ሆኖ ፍትሕን እያገኙ አይደለም፤ አብያተ ክርስቲያናትም በምእመናን ፍልሰት እየተዘጉም እየተቃጠሉም ነው፡፡
ከዚህም ሌላ የሌለን ነገር እንዳለ አስመስሎ ከየአቅጣጫው የሚወረወረው የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል፤ በቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ላይ በዓላማ የተነሡ አካላት የላኳቸው እንዳሉ በሚመስል መልኩ በስመ ተሐድሶ የሚደረገው እንቅስቃሴ የኛው መለያ የሆነውን ንዋየ ቅድሳትና ልብሰ ተክህኖ፣ መዝሙርና ሥርዓተ አምልኮ በመጠቀም ቤተ ክርስቲያናችንን በአደባባይ እየተዳፈረ ይገኛል፡፡
ይህ አላስፈላጊ ተግባር የሀገሪቱን ዜጎች በእኩልነት የሚያስተዳድረውን ሕገ መንግሥት በቀጥታ የሚፃረር ድርጊት ነው፤ ሆኖም በሕግ የሚጠይቅና የሚያስቆም አካል አልተገኘም፤ እኛም ዝምታን የመረጥን መስለናል፡፡ ነገር ግን መፍትሔው ዝምታ ሳይሆን በሕግ አግባብ ነገሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በዘመናችን እየተከሠተ ያለው ችግር ስንዘረዝር ውለን ብናድር መናገሩ በራሱ መፍትሔ ሊያመጣልን አይችልም፤ ጉባኤው ከዚህ በላይ መናገር እንደሚችልም እንገነዘባለን፤ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ የሚችል መደላድል ይህ ጉባኤ በዚህ ስብሰባ ሊተልም ይገባል ብለን ከአደራ ጋር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ
8 months ago
በሊቀ ሰማዕታት በቅዱስ ጊዮርጊስ ዘመን የነበሩና ሰማዕትነት የተቀበሉ፣ ከማዕድ በኋላ ስብሐት ተብሎ ስማቸው ተጠርቶ መጉረስ ሙታንን እንደሚያስምር ቃል ኪዳን የተሰጣቸው አባት ናቸው አባ ቡላ ወይም አቡነ አቢብ፡፡
በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው የታነጹ 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ደግሞ የብዙዎች አባት፣ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድላቸው የተከበረ አባት፣ በትሩፋት የተጋ፣ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት፣ ይላቸዋል፡፡ የተውለዱት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ በሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው፡፡ ወላጆቻቸው እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ልጅ አልነበራቸውም፡፡ በዘመነ ሰማዕታት ከመክስምያኖስ ሸሽተው በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ተወልደዋል፡፡
ሲጸነሱም ወላጆቻቸው የእግዚአብሔር መልአክ በሮማይስጥ ቋንቋ “ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው” የሚል የብርሃን ጽሑፍ በዛፍ ላይ ሲጽፍ ዐይተዋል:: ሕጻኑ ቡላ በዘመነ ሰማዕታት በመወለዱ ለአንድ ዓመት ሳይጠመቅ ቆይቶ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ወደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው፡፡ እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ወላጆቹ ገና በ10 ዓመቱ ተከታትለው ስላረፉ ጎረቤቶች አሳድገውታል፡፡
ሃገረ ገዢው ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ፡፡ ሃገረ ገዢውም ተበሳጭቶ ስፍር ቁጥር የሌለው መከራና ስቃይ አበዛበት፡፡ ይሁንና ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞቶ አስነሳው፡፡ ቅዱስ ቡላ ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ ስለአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለ2ኛ ጊዜ ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ በምንኩስና እንዲኖር መታዘዙን ነገረው፡፡ አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዘወትር ዐርብ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ስጋውን በተለያየ መከራ እየጎዳ ኖሯል፡፡ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል፡፡
በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ ቁልቁል በተወረወረ ጊዜ ሰ ይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና “ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ” አለው፡፡ አቡነ አቢብ ታላቁ አባ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: ከዚህ ዓለም ድካም ሲያርፍም ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና “በእንተ አቡነ አቢብ” ስለ አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፡፡
ገዳማውያን ዓለምን ትተዋልና ቃል ኪዳናቸው ምሕረትን ያስገኛል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና።
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው የታነጹ 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ደግሞ የብዙዎች አባት፣ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድላቸው የተከበረ አባት፣ በትሩፋት የተጋ፣ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት፣ ይላቸዋል፡፡ የተውለዱት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ በሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው፡፡ ወላጆቻቸው እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ልጅ አልነበራቸውም፡፡ በዘመነ ሰማዕታት ከመክስምያኖስ ሸሽተው በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ተወልደዋል፡፡
ሲጸነሱም ወላጆቻቸው የእግዚአብሔር መልአክ በሮማይስጥ ቋንቋ “ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው” የሚል የብርሃን ጽሑፍ በዛፍ ላይ ሲጽፍ ዐይተዋል:: ሕጻኑ ቡላ በዘመነ ሰማዕታት በመወለዱ ለአንድ ዓመት ሳይጠመቅ ቆይቶ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ወደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው፡፡ እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ወላጆቹ ገና በ10 ዓመቱ ተከታትለው ስላረፉ ጎረቤቶች አሳድገውታል፡፡
ሃገረ ገዢው ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ፡፡ ሃገረ ገዢውም ተበሳጭቶ ስፍር ቁጥር የሌለው መከራና ስቃይ አበዛበት፡፡ ይሁንና ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞቶ አስነሳው፡፡ ቅዱስ ቡላ ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ ስለአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለ2ኛ ጊዜ ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ በምንኩስና እንዲኖር መታዘዙን ነገረው፡፡ አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዘወትር ዐርብ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ስጋውን በተለያየ መከራ እየጎዳ ኖሯል፡፡ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል፡፡
በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ ቁልቁል በተወረወረ ጊዜ ሰ ይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና “ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ” አለው፡፡ አቡነ አቢብ ታላቁ አባ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: ከዚህ ዓለም ድካም ሲያርፍም ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና “በእንተ አቡነ አቢብ” ስለ አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፡፡
ገዳማውያን ዓለምን ትተዋልና ቃል ኪዳናቸው ምሕረትን ያስገኛል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና።
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
8 months ago
በሊቀ ሰማዕታት በቅዱስ ጊዮርጊስ ዘመን የነበሩና ሰማዕትነት የተቀበሉ፣ ከማዕድ በኋላ ስብሐት ተብሎ ስማቸው ተጠርቶ መጉረስ ሙታንን እንደሚያስምር ቃል ኪዳን የተሰጣቸው አባት ናቸው አባ ቡላ ወይም አቡነ አቢብ፡፡
በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው የታነጹ 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ደግሞ የብዙዎች አባት፣ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድላቸው የተከበረ አባት፣ በትሩፋት የተጋ፣ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት፣ ይላቸዋል፡፡ የተውለዱት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ በሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው፡፡ ወላጆቻቸው እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ልጅ አልነበራቸውም፡፡ በዘመነ ሰማዕታት ከመክስምያኖስ ሸሽተው በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ተወልደዋል፡፡
ሲጸነሱም ወላጆቻቸው የእግዚአብሔር መልአክ በሮማይስጥ ቋንቋ “ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው” የሚል የብርሃን ጽሑፍ በዛፍ ላይ ሲጽፍ ዐይተዋል:: ሕጻኑ ቡላ በዘመነ ሰማዕታት በመወለዱ ለአንድ ዓመት ሳይጠመቅ ቆይቶ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ወደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው፡፡ እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ወላጆቹ ገና በ10 ዓመቱ ተከታትለው ስላረፉ ጎረቤቶች አሳድገውታል፡፡
ሃገረ ገዢው ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ፡፡ ሃገረ ገዢውም ተበሳጭቶ ስፍር ቁጥር የሌለው መከራና ስቃይ አበዛበት፡፡ ይሁንና ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞቶ አስነሳው፡፡ ቅዱስ ቡላ ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ ስለአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለ2ኛ ጊዜ ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ በምንኩስና እንዲኖር መታዘዙን ነገረው፡፡ አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዘወትር ዐርብ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ስጋውን በተለያየ መከራ እየጎዳ ኖሯል፡፡ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል፡፡
በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ ቁልቁል በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና “ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ” አለው፡፡ አቡነ አቢብ ታላቁ አባ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: ከዚህ ዓለም ድካም ሲያርፍም ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና “በእንተ አቡነ አቢብ” ስለ አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፡፡
ገዳማውያን ዓለምን ትተዋልና ቃል ኪዳናቸው ምሕረትን ያስገኛል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና።
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በሃገራችን በኢትዮጵያ በስማቸው የታነጹ 3ት ታላላቅና ጥንታዊ ገዳማት አሏቸው፡፡ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ሲኸን፤ አቢብ ደግሞ የብዙዎች አባት፣ የመልካም ሥራ ኹሉ ባለቤት ማለት ነው፡፡ ገድላቸው የተከበረ አባት፣ በትሩፋት የተጋ፣ የመልካም ነገሮች ኹሉ አባት፣ ይላቸዋል፡፡ የተውለዱት በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በሮም ሉፊ በሚባል አውራጃ የካቲት 16 ነው፡፡ ወላጆቻቸው እጅግ ጽኑዕ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ልጅ አልነበራቸውም፡፡ በዘመነ ሰማዕታት ከመክስምያኖስ ሸሽተው በበረሃ ሳሉ በመልአክ ብሥራት ተወልደዋል፡፡
ሲጸነሱም ወላጆቻቸው የእግዚአብሔር መልአክ በሮማይስጥ ቋንቋ “ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው” የሚል የብርሃን ጽሑፍ በዛፍ ላይ ሲጽፍ ዐይተዋል:: ሕጻኑ ቡላ በዘመነ ሰማዕታት በመወለዱ ለአንድ ዓመት ሳይጠመቅ ቆይቶ እመቤታችን ለሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ወደ በረሃ ወርዶ እንዲያጠምቀው አዘዝችው፤ ሊያጠምቀው ሲል ሕፃኑ ተነስቶ እጆቹንም ዘርግቶ "አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡ የሕፃኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው፡፡ እነርሱም በዛፉ ላይ የተገለጸውን ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ:: ወላጆቹ ገና በ10 ዓመቱ ተከታትለው ስላረፉ ጎረቤቶች አሳድገውታል፡፡
ሃገረ ገዢው ለጣዖት ስገዱ ብሎ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በሕፃን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ፡፡ ሃገረ ገዢውም ተበሳጭቶ ስፍር ቁጥር የሌለው መከራና ስቃይ አበዛበት፡፡ ይሁንና ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ከሞቶ አስነሳው፡፡ ቅዱስ ቡላ ወደ ሌላ ከሃዲ መኰንን ዘንድ ሄዶ ስለአምልኮ ጣዖቱ ገሠጸው፡፡ ያም ከሃዲ መኰንን ብዙ ካሠቃየው በኋላ ሚያዝያ 18 ቀን ራሱን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለ2ኛ ጊዜ ከሰማይ ወርዶ ቅዱስ ቡላን ከሞት አስነሣው፡፡ ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ በምንኩስና እንዲኖር መታዘዙን ነገረው፡፡ አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዘወትር ዐርብ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን፣ የመድኀኔ ዓለምን ሕማማት እያሰበ ስጋውን በተለያየ መከራ እየጎዳ ኖሯል፡፡ ምንም ነገር ሳይቀምስ፤ መዝሙረ ዳዊትን እየጸለየ ለ42 ዓመታት ጹሟል፡፡
በአንዲት ቀንም ከረጅም ዛፍ ላይ ቁልቁል በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን በረታበትና ገደለው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ተገልጦለት ከሞት አስነሣውና “ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ተባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህ” አለው፡፡ አቡነ አቢብ ታላቁ አባ ዕብሎይን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: ከዚህ ዓለም ድካም ሲያርፍም ገዳሙ በመላእክት ተሞላ:: ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና “በእንተ አቡነ አቢብ” ስለ አባ ቡላ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ያሰበውን ማርልኝ ብለው የለመኑትን ልመና አምላካችን ተቀብሎላቸው ዛሬም በዚህ በቃል ኪዳናቸው የሚያስምሩ ሆነዋል፡፡
ገዳማውያን ዓለምን ትተዋልና ቃል ኪዳናቸው ምሕረትን ያስገኛል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና።
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
Comments