በደራሲና ጋዜጠኛ ዋለልኝ አየለ የተጻፈ “የብሌን አንዳች” የተሰኘ መጽሃፍ ተመረቀ
#ethiopia | ትኩረቱን በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ እና ባህል ላይ ያደረገው “የብሌን አንዳች” ልብ ወለድ መጽሃፍ በ240 ገጾች ታትሞ ለአንባቢያን ቀርቧል፡፡
የመጽሃፉ ምረቃ ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት አዳራሽ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ጸሀፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በመጽሃፉ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ በትውልዶች መካከል የእውቀት ቅብብሎሽ ከሚፈጸምባቸው መንገዶች መካከል አንዱ መጽሃፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የድርሰት ስራዎች ለዲፕሎማሲ ስራዎች ግብዓት መሆናቸውን የተናገሩት አምባሳደር ዲና፤ ወጣቶች ታሪካቸውን መጻፍ አለባቸው ብለዋል፡፡
መጽሀፉን እንዳነበቡት እና የሀገር በቀል እውቀት የመጽሃፉ ትኩረት መሆኑ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ ጸሀፊ ተውኔት አያልነህ ሙላት ናቸው፡፡
እንደ ጸሃፊ ተውኔት አያልነህ ገለጻ፣ “የኢትዮጵያ ትምህርት ስርዓት ከውጭ የተቀዳ በመሆኑ የሀገር በቀል እውቀታችን ጎልቶ እንዳይወጣ አድርጎታል፡፡
ዛሬ የመረቅነው “የብሌን አንዳች” መጽሃፍ በሀገር በቀል እውቀት እና ትምህርት ስርዓታችን ላይ ማተኮሩ ተስፋ ሰጥቶኛል” ብለዋል፡፡
“የብሌን አንዳች” በተሰኘው በዚህ መጽሃፍ ላይ ሒስ ያቀረበው ጋዜጠኛ ታምሩ ከፈለኝ እንዳለው፤ መጽሀፉ በርካታ ጠንካራ ሀሳቦች እንዳሉት ገልፀው፣ የገጸ ባህሪ አወቃቀሩ፣ ውጥነቱ እና የሀሳብ ብዝህነቱን አወድሰዋል፡፡
መጽሀፉ የሚነገር ጠንካራ ታሪክ ከመያዙ ባለፈ የአጻጻፍ ስልቱ እና የቋንቋ አጠቃቀሙን አድንቋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ምክትል ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ከተማ በበኩላቸው፤ ተቋማቸው የኢትዮጵያ ስነ ጽሁፍ ጸሃፊያን ማህጸን መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ደራሲ እና ጋዜጠኛ ዋለልኝ አየለ የዚህ አካል መሆኑን የገለጹት አቶ ፍቃዱ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በኢትዮጵያ ደራሲያንን ያፈራ ተቋም መሆኑንም አክለዋል፡፡
“እነ ብርሃኑ ዘሪሁን፣ ስብሀት ገብረ እግዚያብሔር፣ ጳውሎስ ኞኞ፣ በዓሉ ግርማ እና ሌሎችንም አንጋፋ ጸሃፊዎችን ያፈራው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሁን ደግሞ ጋዜጠኛ ዋለልኝ አየለ ይህን ታሪክ ተቀላቅሏል” ብለዋል፡፡
አቶ ፍቃዱ አክለውም የጋዜጠኛ ዋለልኝ አዲስ መጽሃፍ መጻፍን አድንቀው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዳዲስ ጸሃፊያንን መደገፉን እና ማበርከቱን እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡
በሳሙኤል አባተ
#ethiopia | ትኩረቱን በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ እና ባህል ላይ ያደረገው “የብሌን አንዳች” ልብ ወለድ መጽሃፍ በ240 ገጾች ታትሞ ለአንባቢያን ቀርቧል፡፡
የመጽሃፉ ምረቃ ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት አዳራሽ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ጸሀፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ የዝና ወርቁ፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በመጽሃፉ ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ በትውልዶች መካከል የእውቀት ቅብብሎሽ ከሚፈጸምባቸው መንገዶች መካከል አንዱ መጽሃፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የድርሰት ስራዎች ለዲፕሎማሲ ስራዎች ግብዓት መሆናቸውን የተናገሩት አምባሳደር ዲና፤ ወጣቶች ታሪካቸውን መጻፍ አለባቸው ብለዋል፡፡
መጽሀፉን እንዳነበቡት እና የሀገር በቀል እውቀት የመጽሃፉ ትኩረት መሆኑ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ደግሞ ጸሀፊ ተውኔት አያልነህ ሙላት ናቸው፡፡
እንደ ጸሃፊ ተውኔት አያልነህ ገለጻ፣ “የኢትዮጵያ ትምህርት ስርዓት ከውጭ የተቀዳ በመሆኑ የሀገር በቀል እውቀታችን ጎልቶ እንዳይወጣ አድርጎታል፡፡
ዛሬ የመረቅነው “የብሌን አንዳች” መጽሃፍ በሀገር በቀል እውቀት እና ትምህርት ስርዓታችን ላይ ማተኮሩ ተስፋ ሰጥቶኛል” ብለዋል፡፡
“የብሌን አንዳች” በተሰኘው በዚህ መጽሃፍ ላይ ሒስ ያቀረበው ጋዜጠኛ ታምሩ ከፈለኝ እንዳለው፤ መጽሀፉ በርካታ ጠንካራ ሀሳቦች እንዳሉት ገልፀው፣ የገጸ ባህሪ አወቃቀሩ፣ ውጥነቱ እና የሀሳብ ብዝህነቱን አወድሰዋል፡፡
መጽሀፉ የሚነገር ጠንካራ ታሪክ ከመያዙ ባለፈ የአጻጻፍ ስልቱ እና የቋንቋ አጠቃቀሙን አድንቋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ምክትል ሀላፊ አቶ ፍቃዱ ከተማ በበኩላቸው፤ ተቋማቸው የኢትዮጵያ ስነ ጽሁፍ ጸሃፊያን ማህጸን መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ደራሲ እና ጋዜጠኛ ዋለልኝ አየለ የዚህ አካል መሆኑን የገለጹት አቶ ፍቃዱ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በኢትዮጵያ ደራሲያንን ያፈራ ተቋም መሆኑንም አክለዋል፡፡
“እነ ብርሃኑ ዘሪሁን፣ ስብሀት ገብረ እግዚያብሔር፣ ጳውሎስ ኞኞ፣ በዓሉ ግርማ እና ሌሎችንም አንጋፋ ጸሃፊዎችን ያፈራው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሁን ደግሞ ጋዜጠኛ ዋለልኝ አየለ ይህን ታሪክ ተቀላቅሏል” ብለዋል፡፡
አቶ ፍቃዱ አክለውም የጋዜጠኛ ዋለልኝ አዲስ መጽሃፍ መጻፍን አድንቀው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዳዲስ ጸሃፊያንን መደገፉን እና ማበርከቱን እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡
በሳሙኤል አባተ
9 months ago