Logo
YenetaTube
የሺኖዬ እና ጎቤ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ እየተከበረ ነው

በኦሮሞ ወጣቶች ዘንድ የሚከበረው የሺኖዬ እና ጎቤ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በዓሉ የሚከበረው ያላገቡ ወንድ እና ሴቶች በሚያደርጉት ጨዋታ ነው።

ጎቤ ወጣት ወንዶች የሚጫወቱት ጭፈራ መጠሪያ ሲሆን፤ ሺኖዬ ደግሞ የሴቶች ጭፈራ ነው።

የጎቤ እና የሺኖዬ ባህላዊ ጨዋታ ከጳጉሜን እስከ መስቀል ድረስ የሚከበር ሲሆን፤ ከጭጋጋማዉ የክረምት ወራት ወደ ፀደይ ብርሐን የመሸጋገሪያ ብስራት የሚገለጽበት ነው።

የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል ዕድሜያቸው ከአስራዎቹ መጀመሪያ እስከ ሃያዎቹ አጋማሽ ድረስ ያሉ ልጃገረዶች እና ወጣት ወንዶች ተሰባስበው የሚያከብሩት ባህላዊ ጨዋታ ነው።

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

9 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.