ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ ሊጀመር ነው
ዓለም አቀፍ በረራዎች ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ከክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ ሊጀመር መሆኑን የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ከግል የበረራ ድርጅቶች ጋር በበረራ አገለልግሎት ዙሪያ እየተወያየ ነው።
በባለስልጣኑ የአየር ትራንስፖርትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ ባቀረቡት ሪፖርት በ2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የሃገሪቱ ክልል ኤርፖርቶች ማስስተናገድ እንደሚጀመር ተናግረዋል።
የክልል ኤርፖርቶችን ማስተሳሰ የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር እንዲሁም የደበኛውን እንግልት መቀነስ የሚያስችል ነው ያሉት አቶ እንደሻው፤ ለአብነትም ከሚዛን ቴፒ - ጅማ - ጋምቤላ - አሶሳ እንዲሁም ከድሬደዋ - ሃረር - ባሌሮቤ የተሳሰረ በረራ እንዲኖር ለማድረግ በታሰቡን ገልፀዋል።
ይህም አንድ ሰው በሀገር ውስጥ በረራ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ ለመሄድ የግድ አዲስ አበባ መምጣት እንዳይኖርበት እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
የዓለም አቀፍ በረራዎች ከአዲስ አበባ ኤርፖት በተጨማሪ በክልል አየር ማረፊያዎች ለማስተናገድ መታቀዱንም ተቁመዋል።
ለአብነት ዓለም አቀፍ በረራዎቹን ከባህር ዳር፣ መቀሌ እና ድሬደዋ ቢደረጉ የሃገሪቱን የወጪ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ልማቱን የሚደግፍ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም መንፈሳዊ ጉዞዎችን ከክልል ኤርፖርቶች ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸው የሃጂ ኡምራ ጉዞ፣ ወደ ኢየሩሳሌም፣ ገናን በላሊበላ እና ጥምቀትን በጎንደር ጉዞዎችን ለማስተናገድ ታቅዷል ነው ያሉት።
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
ዓለም አቀፍ በረራዎች ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ከክልል ኤርፖርቶች ማስተናገድ ሊጀመር መሆኑን የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ ከግል የበረራ ድርጅቶች ጋር በበረራ አገለልግሎት ዙሪያ እየተወያየ ነው።
በባለስልጣኑ የአየር ትራንስፖርትና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ ባቀረቡት ሪፖርት በ2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ በረራዎችን ከአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በተጨማሪ በሌሎች የሃገሪቱ ክልል ኤርፖርቶች ማስስተናገድ እንደሚጀመር ተናግረዋል።
የክልል ኤርፖርቶችን ማስተሳሰ የቱሪዝም ፍሰቱ እንዲጨምር እንዲሁም የደበኛውን እንግልት መቀነስ የሚያስችል ነው ያሉት አቶ እንደሻው፤ ለአብነትም ከሚዛን ቴፒ - ጅማ - ጋምቤላ - አሶሳ እንዲሁም ከድሬደዋ - ሃረር - ባሌሮቤ የተሳሰረ በረራ እንዲኖር ለማድረግ በታሰቡን ገልፀዋል።
ይህም አንድ ሰው በሀገር ውስጥ በረራ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ ለመሄድ የግድ አዲስ አበባ መምጣት እንዳይኖርበት እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
የዓለም አቀፍ በረራዎች ከአዲስ አበባ ኤርፖት በተጨማሪ በክልል አየር ማረፊያዎች ለማስተናገድ መታቀዱንም ተቁመዋል።
ለአብነት ዓለም አቀፍ በረራዎቹን ከባህር ዳር፣ መቀሌ እና ድሬደዋ ቢደረጉ የሃገሪቱን የወጪ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ልማቱን የሚደግፍ ነው ብለዋል።
በተጨማሪም መንፈሳዊ ጉዞዎችን ከክልል ኤርፖርቶች ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸው የሃጂ ኡምራ ጉዞ፣ ወደ ኢየሩሳሌም፣ ገናን በላሊበላ እና ጥምቀትን በጎንደር ጉዞዎችን ለማስተናገድ ታቅዷል ነው ያሉት።
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
10 months ago