Logo
Getu Temesgen
ከሁለት ሳምንት በኋላ ከግብፅ እና ሴራሊዮን ጋር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ያለበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ዝግጅቱን ጀምሯል
#ethiopia | ዋልያዎቹ ዛሬ ከቀኑ 10:00 እስከ 11:00 በአዲስ አበባ ስታዲየም ልምምዳቸውን ሰርተዋል።

እንዲሁም ከ " Road to 2029 " ፕሮጀክት ሰባት ታዳጊ ተጨዋቾች ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛሉ።

በሌላ በኩል በአሜሪካ ይገኙ የነበሩት :-

- ከንአን ማርክነህ
- ቢንያም በላይ
- ራምኬል ጄምስ
- ሀብታሙ ተከሰተ ጨምሮ በሀገር ውስጥ የሚገኙት ሱሌማን ሀሚድ እና ረመዳን የሱፍ ከነገ ጀምሮ ቡድኑን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ በቀን ሁለት ጊዜ የአካል ብቃት እና ታክቲካል ዝግጅቶችን እንደሚያደርግ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ተናግረዋል።

በቀጣይ ቀናት ሁለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን ለማድረግ መታሰቡንም አሰልጣኙ ጠቁመዋል።
#ts #sport #gtmc

12 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.