Logo
FIDEL POST NEWS
በሕንፃዎችና በቤቶች ውስጥ የፀሐይ ኃይል መጠቀም አስገዳጅ ሊሆን ነው

ኢትዮጵያ ያላትን የፀሐይ ኃይል ለመጠቀም በሁሉም ሕንፃዎችና ቤቶች ውስጥ የፀሐይ ኃይል መጠቀም በሒደት አስገዳጅ እንደሚሆን ተገለጸ፡፡ይህ የተገለጸው የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከኢንተርናሽናል ሶላር አሊያንስ (International Solar Alliance) ጋር የፀሐይ ኃይል በጋራ ለማልማት የሚያስችል ስምምነት ነሐሴ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ሲፈራረሙ ነው፡፡

‹‹ኢትዮጵያ ከፍተኛ የፀሐይ ኃይል አላት›› ያሉት የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ደኤታ ሡልጣን ወሊ (ኢንጂነር)፣ ይህን አቅም ጥቅም ላይ ለማዋል ከዚህ ቀደም አለመሠራቱን፣ ለዚህም ሲባል በሒደት በእያንዳንዱ ቤትና ሕንፃ ጣሪያ የፀሐይ ኃይል ቴክኖሎጂ እንደሚገጠም አስታውቀዋል፡፡

ተጨማሪ : https://ethiopianreporter....
10 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.