Logo
FIDEL POST NEWS
ኢትዮጵያ የተቀበሩ ፀረ ሰው ፈንጂዎችን ለማስወገድ የጊዜ ገደቡ ለአራተኛ ጊዜ እንዲራዘምላት ጥያቄ አቀረበች!

 በጄኔቫ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት፣ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በጦርነት ወቅት ተቀብረው የቀሩ የፀረ ሰው ፈንጂ ቅሪቶችን ለማስወገድ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ለአራተኛ ጊዜ እንዲራዘም ጥያቄ አቀረበ፡፡

እ.ኤ.አ. በ2004 ኢትዮጵያ ያፀደቀችውና የኦታዋ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን እ.ኤ.አ. በ1997 የፀደቀውን የፀረ ሰው ፈንጂዎች ጥቅም፣ ምርት፣ ግብይትና ክምችትን ለማስወገድና ለማገድ የወጣ ስምምነት መፈረሟ ይታወሳል፡፡

ኢትዮጵያ በስምምነቱ አንቀጽ 5 መሠረት በየትኛውም የአገሪቱ አካባቢዎች ያሉ ፀረ ሰው ፈንጂዎችን ማስወገድ፣ ወይም መወገዳቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዕርምጃዎችን የመውሰድ ግዴታ እንዳለባት ተደንግጓል፡፡

https://ethiopianreporter....
10 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.