Logo
FIDEL POST NEWS
" የአደጋዉን ትክክለኛ መንስኤ መራማሪ ፖሊስ አባላህ እያጣሩ ነው " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አጠገብ በሚገኘዉ አትነት የገበያ ማዕከል ጀርባ ዛረ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።

በሕብረተሰቡና በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እሳት ማጥፊያ መኪኖች ታግዞ እሳቱ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉን በሀዋሳ ከተማ ፖሊስ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ምክትል ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ዕድገት እንዳለለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" የአደጋዉን ትክክለኛ መንስኤ መራማሪ ፖሊስ አባላት እያጣሩ " ነው ያለቱ ም/ኮማንደሩ " በአደጋዉ ከዋናዉ ህንፃ ጀርባ የነበሩ ሁለት ተያያዥ ኮንተነር ሱቆች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል ፤ በሕብረተሰቡና የፀጥታ ሃይሉ ርብርብ እሳቱ ወደ አትነት የገበያ ማዕከል ዋናዉ ሕንፃና ወደ ቅዱስ ገበርኤል ትምህርት ቤት እንዳይዛመት ተደርጎ በቁጥጥር ስር ዉሏል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawssa

tikvahethiopia
12 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.