ከትራምፕ ጋር በገቡት ዕልህ ሕንዳዊያን የሀገራቸውን ምርት ብቻ እንዲገዙ ትዕዛዝ ተሰጣቸው
አሜሪካ በሕንድ ላይ የጣለችውን ታሪፍ ተከትሎ ዕልህ የተጋቡት የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ናሬንድራ ሞዲ ሕንዳዊያን የሀገራቸውን ምርት ብቻ እንዲገዙ ትዕዛዝ አዘል መልዕክት አስተላለፉ።
የትራምፕ አስተዳደር ህንድ ወደ አሜሪካ በምትልካቸው ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ከጣለ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን በመረዳት የሕንድ ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት የገለጹት።
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ዛቻን በመቃወም ህዝቡ የሀገር ውስጥ እቃዎችን እንዲገዛ ያሳሰቡ ሲሆን፤ አስተዳደሩ የሩሲያ ዘይት መግዛቱን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰሜናዊ ኡታር ፕራዴሽ በተካሄደው ሰልፍ ላይ የዓለም ኢኮኖሚ በአስፈሪ ሂደቶች ውስጥ እያለፈ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ህንድ የሩስያ ዘይት ግዢን ከቀጠለች ዋይት ሀውስ ተጨማሪ እርምጃ እንደሚወስድ እያስፈራራ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አሁን የምንገዛው ማንኛውም ምርት በህንድ ላብ የተሰሩትን ብቻ መሆን አለበት” ብለዋል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ህንድን የብሪክስ ቡድን አባል መሆኗን እና ከሩሲያ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላት በመተቸት “የሞተ ኢኮኖሚያቸውን በአንድ ላይ ሊያወርዱ ይችላሉ” ሲሉ ተችተዋል።
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
አሜሪካ በሕንድ ላይ የጣለችውን ታሪፍ ተከትሎ ዕልህ የተጋቡት የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ናሬንድራ ሞዲ ሕንዳዊያን የሀገራቸውን ምርት ብቻ እንዲገዙ ትዕዛዝ አዘል መልዕክት አስተላለፉ።
የትራምፕ አስተዳደር ህንድ ወደ አሜሪካ በምትልካቸው ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ከጣለ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን በመረዳት የሕንድ ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት የገለጹት።
የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የዶናልድ ትራምፕ የታሪፍ ዛቻን በመቃወም ህዝቡ የሀገር ውስጥ እቃዎችን እንዲገዛ ያሳሰቡ ሲሆን፤ አስተዳደሩ የሩሲያ ዘይት መግዛቱን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰሜናዊ ኡታር ፕራዴሽ በተካሄደው ሰልፍ ላይ የዓለም ኢኮኖሚ በአስፈሪ ሂደቶች ውስጥ እያለፈ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
ህንድ የሩስያ ዘይት ግዢን ከቀጠለች ዋይት ሀውስ ተጨማሪ እርምጃ እንደሚወስድ እያስፈራራ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አሁን የምንገዛው ማንኛውም ምርት በህንድ ላብ የተሰሩትን ብቻ መሆን አለበት” ብለዋል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ህንድን የብሪክስ ቡድን አባል መሆኗን እና ከሩሲያ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላት በመተቸት “የሞተ ኢኮኖሚያቸውን በአንድ ላይ ሊያወርዱ ይችላሉ” ሲሉ ተችተዋል።
Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
10 months ago