Logo
Getu Temesgen
ሀሴት ከፕሬዝደንቷ ጋር ተወያየች
#ethiopia | ‹‹ሚስ አፍሪካ›› ሀሴት ደረጄ ከታንዛኒያ ፕሬዝደንት ጋር ውይይት አደረገች፡፡ የታንዛኒያ ፕሬዝደንት ሚስ ሳሚያ ሱሉ ሀሰን በዛሬው እለት በፅህፈት ቤታቸው የ2025 ሚስ ወርልድ አሸናፊዎችን አነጋግረዋል፡፡

ውድድሩን በ1ኝነት ያሸፈችው ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሳቻታና በውድድሩ 2ተኛ የወጣችውና ከአፍሪካ አንደኛ ቆንጆ የተባለችው ኢትዮጵያዊቷ ሀሴት ደረጀ ከፕሬዝደንቷ ጋር ተገናኝተው ውይይት ማድረጋቸውን የታንዛኒያ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል፡፡

እነዚህ 2 ቆነጃጅት ወደዚያው የተጓዙት ከሚስ ወርልድ ካምፓኒ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጁሊያ አቭሊን ጋር ነው፡፡ በውይይታቸውም የቀጣዩን አመት ማለትም የ2026 ሚስ ወርልድ ውድድር ታንዛኒያ በምታዘጋጅበት ሁኔታ ላይ መነጋገራቸውን መረጃው ገልጿል፡፡ #zehabesha

1 year ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.